ሊቨርፑል ዌስትሃምን አሸነፈ
በ13ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ዌስትሃም ዩናይትድን በማሸነፍ በሊጉ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል።
በለንደን ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የመርሲሳይዱ ክለብ መዶሻዎቹን 2 ለ 0 በማሸነፍ ወሳኝ ድል አስመዝግቧል።
የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ጎሎች አሌግዛንደር ኢሳቅ እና ኮዲ ጋግፖ አስገኝተዋል።
በጨዋታው በዌስትሃም ዩናይትድ በኩል ሉካስ ፓኩዌታ በሁለት የማስጠንቀቂያ ቢጫ ቀይ ካርድ ተመልክቶ ከሜዳ ወጥቷል።
አሌግዛንደር ኢሳቅ በሊቨርፑል የመጀመሪያ የፕሪሚዬር ሊግ ጎሉን አስቆጥሯል።
ሊቨርፑል ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 21 በማድረስ 8ኛ ደረጃን ይዟል።
8ኛ የሊግ ሽንፈቱን ያስተናገደው ዌስትሃም በአንፃሩ በ11 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በሌሎች ጨዋታዎች ብራይተን ከሜዳው ውጪ ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 በሆነ ተመሳሳይ ውጤት ረቷል።
አስቶንቪላ ደግሞ በሜዳው ቡባካር ካማራ ባስቆጠራት ብቸኛ ጎል ዎልቭስን በማሸነፍ 3ኛ ደረጃን መያዝ ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ