አሌክሳንደር አርኖልድ ለሁለት ወራት ከሜዳ የሚያርቀውን ጉዳት አስተናገደ
የሪያል ማድሪዱ የቀኝ መስመር ተከላካይ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ ለሁለት ወራት ከሜዳ የሚያርቀውን ጉዳት ማስተናገዱ ተገልጿል።
እንግሊዛዊው ተጫዋች ጉዳት ያስተናገደው ትናንት ምሽት ሪያል ማድሪድ ከሜዳው ውጪ አትሌቲክ ቢልባኦን 3ለ0 በረታበት ጨዋታ ነው።
ተጫዋቹ በ53ኛው ደቂቃ ተቀይሮ ከሜዳ ከወጣ በኋላ በተደረገለት ምርመራ የጡንቻ ጉዳት እንዳጋጠመው ክለቡ አሳውቋል።
ጉዳቱን ተከትሎ አሌክሳንደር አርኖልድ ቢያንስ ለሁለት ወራት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ማርካ አስነብቧል።
በእነዚህ ጊዜያት ውስጥም 10 የሚሆኑ ጨዋታዎች ሊያመልጡት እንደሚችል ተመላክቷል።
የ27 ዓመቱ ተጫዋች አሌክሳንደር አርኖልድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የልጅነት ክለቡን ሊቨርፑልን ለቆ ወደ ሪያል ማድሪድ መዛወሩ የሚታወስ ነው።
ሎስብላንኮዎቹን ከተቀላቀለ ወዲህ ለ3ኛ ጊዜ ነው ጉዳት ያስተናገደው።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ