ባለፉት 7 አመታት በአንድ ጀምበር ብቻ ከ7 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በ56 ሚሊዮን የተለያዩ ጠቀሜታዎች ባሏቸዉ ችግኞች መሸፈን መቻላቸዉን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
በዛሬዉ ዓለት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ በሚገኘዉ ሀጫሞ ቀበሌ ገርባ ተፋሰስ ተካሂዷል።
በዘንድሮው የአንድ ጀምበር መርሀ ግብር ላይ በዞኑ ከ1.5 ሚሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል እየተሰራ ይገኛል።
እስከአሁን እየተተከሉ የሚገኙ ችግኞች ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ፣ የቡና፣ ቅመማ ቅመም፣ መኖ እና የደን ችግኞች ሲሆኑ የአከባቢን ገጽታን ከመቀየርና ከመጠበቅ ባሻገር ለኢንዱስትሪ ግብኣት ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው፡፡
እንደዞን ባለፉት ሰባት ተከታታይ ዓመታት ለአረንጓዴ አሻራ ተከላ በተሠጠው ልዩ ትኩረት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በአማካይ 362,500 ለተከላ የደረሰ ሰው በማሳተፍ በተለዩ የተከላ ቦታዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ከ510,204,338 በላይ ችግኖች 94,925 ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል፡፡
ባለፈው ዓመት የተተከለውን ችግኝ የእንክብካቤ ስራዉን አጠናቀክሮ በማስቀጠል ጽድቀትን በአማካይ 88.81 በመቶ ማድረስ መቻሉ ተጠቁሟል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ ሥራም የዞኑ የደን ሽፋን ወደ 23.2 በመቶ እንዲሻሻል አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተገልጿል፡፡
በመርሀ ግብሩ ላይ የተለያዩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪ በነቂስ በመዉጣት አሻራቸዉን አኑረዋል።
ዘጋቢ፡ ፍሬህወት ኡሹሌ

More Stories
የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የአካባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባሻገር የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና ለቀጣይ ትውልድ አረንጓዴ አካባቢ ለማውረስ ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል
ዛሬ የምንተክለው እያንዳንዱ ችግኝ የነገዋን አረንጓዴ፣ ለምለም፣ የተደላደለችና የበለጸገች ከምባታን የመገንቢያ ጠንካራ መሰረት የምንጥልበት ነው አሉ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ