ዊሊያም ሳሊባ ከለንደን ደርቢው ጨዋታ ውጪ ሆነ
ፈረንሳዊው የመሀል ስፍራ ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ አርሰናል በሰሜን ለንደን ደርቢ ከቼልሲ ጋር ከሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ውጪ ሆኗል።
ዊሊያም ሳሊባ በልምምድ ወቅት ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከጨዋታው ውጪ መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ አዳዲስ ፈራሚዎቹ ክርስቲያን ሞስኬራ እና ፒዬሮ ሂንካፒዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጣምረው ይጫወታሉ።
በሌላ በኩል ቪክቶር ግዮኬሬሽ ከበርንሌይ ጨዋታ በኋላ እንዲሁም ጋብርኤል ጄሱስ ከጥር ወር በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በተጠባባቂ ወንበር ላይ ተቀምጠው ጨዋታውን ይጀምራሉ።
በቼልሲም በኩል ከሁለት ወራት በኋላ ወደ ሜዳ የተመለሰው ኮል ፓልመር ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ ጨዋታውን ያደርጋል።
ለ212ኛ ጊዜ የሚካሄደው የለንደን ደርቢ ጨዋታ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ይደረጋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት