ዊሊያም ሳሊባ ከለንደን ደርቢው ጨዋታ ውጪ ሆነ
ፈረንሳዊው የመሀል ስፍራ ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ አርሰናል በሰሜን ለንደን ደርቢ ከቼልሲ ጋር ከሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ውጪ ሆኗል።
ዊሊያም ሳሊባ በልምምድ ወቅት ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከጨዋታው ውጪ መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ አዳዲስ ፈራሚዎቹ ክርስቲያን ሞስኬራ እና ፒዬሮ ሂንካፒዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጣምረው ይጫወታሉ።
በሌላ በኩል ቪክቶር ግዮኬሬሽ ከበርንሌይ ጨዋታ በኋላ እንዲሁም ጋብርኤል ጄሱስ ከጥር ወር በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በተጠባባቂ ወንበር ላይ ተቀምጠው ጨዋታውን ይጀምራሉ።
በቼልሲም በኩል ከሁለት ወራት በኋላ ወደ ሜዳ የተመለሰው ኮል ፓልመር ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ ጨዋታውን ያደርጋል።
ለ212ኛ ጊዜ የሚካሄደው የለንደን ደርቢ ጨዋታ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ይደረጋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።