አርባምንጭ ከተማ በሸገር ከተማ ተሸነፈ

አርባምንጭ ከተማ በሸገር ከተማ ተሸነፈ

በ6ኛ ሳምንት የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ አርባምንጭ ከተማ በሸገር ከተማ ተሸንፏል።

ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሸገር ከተማ አዞዎቹን 1ለ0 አሸንፏል።

የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ጎል ሄኖክ አዱኛ በፍፁም ቅጣት አስቆጥሯል።

በጨዋታው በአርባምንጭ ከተማ በኩል አካሉ አቱሞ በሁለት ቢጫ ቀይ ካርድ ተመልክቷል።

አርባምንጭ ከተማ በዚህ የውድድር ዓመት 3ኛ የሊግ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

ሁለተኛ ድሉን ያስመዘገበው ሸገር ከተማ ነጥቡን 8 በማድረስ 10ኛ ደረጃን ይዟል።

እስካሁን አንድም የሊግ ጨዋታ ያላሸነፈው አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ በ3 ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ