ቼልሲ በርንሌይን በማሸነፍ ተከታታይ ድል አስመዘገበ
በ12ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ቼልሲ በርንሌይን 2ለ0 በማሸነፍ 3ኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።
በተርፍ ሙር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለቼልሲ የማሸነፊያ ግቦችን ፔድሮ ኔቶ እና ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከመረብ አሳርፈዋል።
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ከአራት ዓመታት በኋላ 3 ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን ጎል ሳይቆጠርበት ማሸነፍ ችሏል።
ቼልሲ በሁሉም ውድድሮች ባለፉት 5 ተከታታይ ጨዋታዎች አልተሸነፈም።
ቼልሲ ማሸነፉን ተከትሎ በ23 ነጥብ 2ኛ ደረጃን ይዟል።
8ኛ የሊግ ሽንፈቱን ያስተናገደው በርንሌይ በአንፃሩ በ10 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የጎዳና ሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል