ማህበሩ ዓላማውን እና የስራ እንቅስቃሴውን በተመለከተ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይና የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ወዳጆ፤ ማህበሩ ለህብረተሰቡ የሚያደርገውን ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲያጠናክር አመራሩ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
የስራ እንቅስቃሴውን ለመደገፍ የከተማ አስተዳደሩ በቅርቡ የ1.2 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን አቶ ዘለቀ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ጋኖ ገረመው፤ ማህበሩ በኢትዮጵያ ላለፉት 90 ዓመታት በርካታ ሰብአዊ ድጋፎችን ሲያደርግ እንደቆየ ገልጸዋል።
ዋና ዓላማው በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋዎች በሰዎች ላይ የሚደርሱ ችግሮችን ማቃለል ነው ያሉት አቶ ጋኖ፤ እንቅስቃሴውን ይበልጥ ለማጠናከር የሁሉም ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደም ባንክና የአምቡላንስ አገልግሎቶችን በመስጠት እንዲሁም የመጀመሪያ የነርሶችን ኮሌጅ በመመስረት ጠቃሚ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል።
ማህበሩ እያከናወነ የሚገኘውን የሰብዓዊ ድጋፍ ስራ ለማስቀጠል ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በስልጠና መድረኩ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሂማኒቴሪያን ዲፕሎማሲና የኮሙኒኬሽን ሰርቪስ ከፍተኛ ባለሙያ በአቶ ንጉሴ አብዬ የስልጠና ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የትምህርት ጥራት፣ ውጤትና ተደራሽነት ዙሪያ ማነቆ የሆኑ ጉዳዮችን ለመፍታት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ