የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ
ሀዋሳ፡ የካቲት 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ አካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ እንደገለፁት፥ በቢሮ ሥር ያሉ የዘርፍ የሥራ ክፍሎች በተናበበና በተቀናጀ መልኩ ሥራ ቆጥረው ውጤት እንዲያስመዘግቡ እየተሠራ መሆኑ ተመላክቷል።
በክልሉ ያሉ መዋቅሮች በዚህ ልክ እንዲተገብሩ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ሲሆን፥ የመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረቡ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዘርፉ አፈፃፀሞች ላይ ክፍቶችን ለማረም እንዲሠሩ አቶ መና አሳስበዋል።
የወባ ወረርሽኝ በተለያየ ጊዜ በክልሉ ስር የሚስተዋልበት ሁኔታ ስለመኖሩና ቢሮ ይህንን በመቆጣጠር ሂደት በሰጠው ልዩ ትኩረት ውጤት መመዝገቡን አቶ መና መኩሪያ ጠቅሰው፥ ሆኖም አሁንም በወባ በሽታ ዙሪያ ብዙ ሥራን ይጠይቃል ብለዋል።
በሁሉም የጤና አገልግሎት ዘርፎች አሁን ያለው አፈፃፀም ዓመቱ ሲጠቃለል በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዲመዘገብ የመድረኩ ተሳታፊዎች በቁርጠኝነት ሊሠሩ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ከቀረበው የየዘርፉ የጤና አገልግሎቶች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ የሚያሳይ መረጃ ማግኘታቸውን ጠቅሰው፥ ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱ ያለባቸውን ክፍተት ለማረምና ለህዝቡ ተጠቃሚነት እንደሚሠሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ወጣቶች ግጭትን በመከላከል ረገድ ሊኖራቸው የሚገባ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በመመዝገብ የሚፈልገውን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጥ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ጥሪ አቀረበ
የፓርቲው የምርጫ ማኒፌስቶ የትላንት ጉድለቶችን በማከም ዛሬን በሚገባ ተጠቅሞ ነገን በመተለም የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልፅግና በማረጋገጥ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ማድረስ መሆኑን የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ