የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ

የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ

ሀዋሳ፡ የካቲት 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ አካሂዷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራምና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ እንደገለፁት፥ በቢሮ ሥር ያሉ የዘርፍ የሥራ ክፍሎች በተናበበና በተቀናጀ መልኩ ሥራ ቆጥረው ውጤት እንዲያስመዘግቡ እየተሠራ መሆኑ ተመላክቷል።

በክልሉ ያሉ መዋቅሮች በዚህ ልክ እንዲተገብሩ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ሲሆን፥ የመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረቡ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዘርፉ አፈፃፀሞች ላይ ክፍቶችን ለማረም እንዲሠሩ አቶ መና አሳስበዋል።

የወባ ወረርሽኝ በተለያየ ጊዜ በክልሉ ስር የሚስተዋልበት ሁኔታ ስለመኖሩና ቢሮ ይህንን በመቆጣጠር ሂደት በሰጠው ልዩ ትኩረት ውጤት መመዝገቡን አቶ መና መኩሪያ ጠቅሰው፥ ሆኖም አሁንም በወባ በሽታ ዙሪያ ብዙ ሥራን ይጠይቃል ብለዋል።

በሁሉም የጤና አገልግሎት ዘርፎች አሁን ያለው አፈፃፀም ዓመቱ ሲጠቃለል በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዲመዘገብ የመድረኩ ተሳታፊዎች በቁርጠኝነት ሊሠሩ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ከቀረበው የየዘርፉ የጤና አገልግሎቶች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ የሚያሳይ መረጃ ማግኘታቸውን ጠቅሰው፥ ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱ ያለባቸውን ክፍተት ለማረምና ለህዝቡ ተጠቃሚነት እንደሚሠሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን