የእንስሳትን ጤና መጠበቅ የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ መሆኑን በኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የእንስሳትን ጤና መጠበቅ የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ ነው ሲል በኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ የእንስሳት ጤና ቁጥጥርና በሽታ መከላከል አስታወቀ፡፡
የኮሬ ዞን አርሶ አደሮች እንስሳትን በማስከተብ በሽታን መከላከል መቻላቸውን ገልፀዋል።
የእንስሳት ጤና ከሚጠበቅበት መንገድ አንዱ ተከታታይ ክትባት ሲሆን ሰዎች የእንስሳትን ተዋጽኦ ተጠቃሚ በመሆናቸው ጤናቸውን መጠበቅ የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ እንደ ሆነ ነው በኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ የእንስሳት ጤና ቁጥጥርና በሽታ መከላከል ቡድን መሪ ዶክተር ዓለሙ ጥላሁን የተናገሩት።
በዓለም አቀፍ ደረጃ 71 በመቶ በኢትዮጵያ 51 በመቶ በላይ በሽታ ከእንስሳት ወደ ሰው እንደሚተላለፍ ጥናቶች ያረጋግጣሉ ያሉት ዶክተር ዓለሙ፥ ከበሽታ ነፃ የሆነ እንስሳትን በመፍጠር የሰው ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ወቅቱን ጠብቆ የሚቀሰቀሱ በሽታዎችን ለመከላከል በጊዜ ሰሌዳ ክትባት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።
የእንስሳትን ሙሉ ጤና ለመጠበቅ ንጽህናውን መጠበቅ፣ በቂ መኖ ማቅረብና እንስሳቱ ሲታመሙ በሰለጠኑ ባለሙያዎች ብቻ ማሳከም እንደሚጠበቅባቸው ነው የተናገሩት።
አርሶአደር ተስፋዬ ሞቻ እና በዛብህ ቶሬ ከዚህ ቀደም ከብቶቻቸው በወረርሽኝ በሽታ ሲጠቁ እንደነበር ገልጸው ተከታታይ ክትባት መሰጠት ከጀመረ ወዲህ የእንስሳት ጤና መጠበቁን ተናግረዋል።
አክለውም አርሶአደሮቹ ከልምድ ህክምና ወጥተው በሰለጠነ ባለሙያ በማሳከምና በቂ መኖ በማቅረብ የእንስሳቱን ተዋጽኦ ማሳደጋቸውን ነው የገለጹት።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ