ወ/ሮ ሰላማዊት ማሞ የሸካ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ
የሸካ ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዞኑ ቴፒ ከተማ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በሸካ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አለሙ አቅራቢነት ወ/ሮ ሰላማዊት ማሞ የሸካ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሆነው እንዲሾሙ ባቀረቡት መሰረት በምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አበበ ማሞ አቅራቢነት ሌሎችም ዕጩዎች በአባላቱ ሙሉ ድምፅ ሹመታቸው የፀደቀ ሲሆን ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው የኃላፊነት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በዚህም መሠረት ምክትል አፈ ጉባኤዋን ጨምሮ
አቶ ተሾመ አስረስ – የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት
አቶ ሙሉዓለም ስለሺ – የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሁም
አቶ ደምስስ አየለ – የማሻ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾሙ ሲሆን በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
ዘጋቢ: አስቻለው አየለ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ