ወ/ሮ ሰላማዊት ማሞ የሸካ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ
የሸካ ዞን ምክር ቤት 5ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዞኑ ቴፒ ከተማ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በሸካ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አለሙ አቅራቢነት ወ/ሮ ሰላማዊት ማሞ የሸካ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሆነው እንዲሾሙ ባቀረቡት መሰረት በምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አበበ ማሞ አቅራቢነት ሌሎችም ዕጩዎች በአባላቱ ሙሉ ድምፅ ሹመታቸው የፀደቀ ሲሆን ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው የኃላፊነት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በዚህም መሠረት ምክትል አፈ ጉባኤዋን ጨምሮ
አቶ ተሾመ አስረስ – የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት
አቶ ሙሉዓለም ስለሺ – የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሁም
አቶ ደምስስ አየለ – የማሻ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾሙ ሲሆን በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
ዘጋቢ: አስቻለው አየለ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ