የክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ይገኛል
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት 24ኛ መደበኛ ስብሰባውን በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት በማካሄድ ላይ ይገኛል።
መስተዳድር ምክር ቤቱ በዚሁ በ24ኛ መደበኛ ስብሰባው፡-
የክልሉን መንግስት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም በመገምገማ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ፣ በታችኛው የአስተዳደር እርከን የአስፈጻሚ አካላት የስልጣን እና ተግባር የመዋቅር ማሻሻያ እንዲሁም የቀረቡ የተለያዩ ረቂቅ ደንቦች መርምሮ ማፅደቅን ጨምሮ ሌሎች የካቢኔ ውሳኔ የሚሹ ተያያዥ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ