የፕሪሚዬር ሊጉ የመክፈቻ ሳምንታት ጨዋታዎች በሀዋሳ እንደሚካሄዱ ተገለፀ
የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ የምድብ አንድ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ጨዋታዎች በሀዋሳ ከተማ እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
ቀደም ብሎ በወጣው መርሐግብር የፕሪሚዬር ሊጉ የመጀመሪያ ዘጠኝ ሳምንታት ውድድር በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ እንደሚደረግ መገለፁ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ድሬዳዋ ከተማ ውድድሩን ለማስተናገድ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠ በመሆኑና ዝግጁ አለመሆኑን በመግለፁ ድሬዳዋ ላይ ሊካሄዱ የነበሩ ጨዋታዎች ወደ ሀዋሳ ከተማ መዛወራቸውን የሊጉ አክሲዮን ማህበር አሳውቋል።
አክሲዮን ማህበሩ አያይዞም የተስተካከለው የጨዋታ መርሐግብር በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ብሩኖ ፈርናንዴዝ ወደ ሳውዲ ፕሮ ሊግ የማቅናት ፍላጎት እንደሌለው ተገለፀ
የሰርከስ ስፖርት ሳይንሳዊ ጥበቡን ጠብቆ ለማጎልበት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ
አሰልጣኝ ስቴቨን ጄራርድ ወደ ቀድሞ ክለቡ ለመመለስ በንግግር ላይ ነው