የብልጽግና ፓርቲ በየወቅቱ ለአባላቱ የሚያዘጋጃቸው የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የመፈፀም አቅማቸውን እያጎለበተ መሆኑን የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር አባል አመራሮች ተናገሩ።
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተሻሻሉ መመሪያዎች ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው መክፈቻ የይርጋጨፌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ኦብሰ፤ የብልጽግና ፓርቲ ውስጣዊ እና ዉጫዊ ፈተናዎችን ተቋቁሞ በርካታ ድሎችን እያስመዘገበ እንደሚገኝና ድሉን ለማስቀጠል የአባሉን አቅም የሚያጎለብቱና ውስጣዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ መሰል ስልጠናዎች ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ስልጠናው ቀጣይነት ያለውና ሁሉም አባል ሀገሪቱ ያለችበትን አሁናዊ ነባራዊ ሁኔታን በመገንዘብ እንደሀገር ለተያዙ ግዙፍ እቅዶች ስኬት የበኩሉን እንዲወጣ ከመርዳቱም ባሻገር፤ የፓርቲውን የአሠራር ሥርዓት ጠንቅቆ በማወቅ የጋራ ትርክትን መገንባት በሚያስችሉ እሳቤዎች ላይ አበክሮ ለመሥራት አጋዥ ኃይል መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በስልጠናው የተሳተፉ የፓርቲው አባላት፤ ፓርቲው ዓለም አቀፋዊ እውነታዎችን በመገንዘብ የኢትዮጵያን የተደማጭነት አቅም ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን እና መሰል ስልጠናዎች ስለፓርቲው የአሠራር ደንብና መመሪያዎች ያላቸውን ግንዛቤ ከፍ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ያገኙትን ስልጠና ወደ ውጤት ለመቀየር ተግተው እንደሚሠሩ የጠቆሙት የስልጠናው ተሳታፊዎች፤ በቀጣይ ያገኙትን ግንዛቤ ለተቀሩት አባላት የማስረጽ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ አስታውቀዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ