የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ከ8 ሺህ 4 መቶ በላይ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታዉቋል።
አንዳንድ የአርባምንጭ ከተማ ነጋዴዎች፤ በህጋዊ መንገድ በተለያዩ የንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርተው እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው ህጋዊነትን በመጣስ የሚሰሩ አንዳንድ ነጋዴዎች በሀገርና በህዝብ ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተጽዕኖዎች ከፍ ያለ እንደሆነ ተናግረዋል።
የሚስተዋለውን ህገወጥ ተግባር ለመከላከል በርካታ የቁጥጥር እና የክትትል ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን ተናግረዋል።
ህጋዊ የንግድ ስርዓትን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ በነበሩት ግለሰቦችና የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃዎች እንደተወሰዱ መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት የምርት አቅርቦት በማሳደግና የሰንበት ገበያዎችን በተጨማሪ በማቋቋም ለህብረተሰቡ መሰረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችንና የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የሚስተዋለውን የኑሮ ዉድነት ለማረጋጋት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን ጠቁመዋል።
ዘጋቢ፡ ስምረት አስማማው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ