ክርስቲያኖ ሮናልዶ የክብር ሽልማት ተሰጠው
ፖርቹጋላዊው ኮከብ ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች በመባል የክብር ሽልማት ተሰጥቶታል።
የአምስት ጊዜ የባሎንዲኦር አሸናፊው ሮናልዶ ይህ የክብር ሽልማት የተሰጠው ከፖርቹጋል እግርኳስ ፌዴሬሽን ነው።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከሽልማቱ በኋላ በሰጠው አስተያየት በርካታ ሽልማቶች ያሉት ቢሆንም ይሄኛው ሽልማት ግን የተለየ መሆኑን ተናግሯል።
የ40 ዓመቱ ተጫዋች ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን እስካሁን በ223 ጨዋታዎች 141 ጎሎችን በማስቆጠር በመላው ዓለም በብሔራዊ ደረጃ የምንጊዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ መሆኑ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
በክልሉ የተጀመረውን የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከግጭት የጸዳ አካባቢ ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላም እና ፀጥታ ቢሮ አሳሰበ
በዘመናዊ መንገድ ንብ የማነብ ስራ በመጀመር ውጤታማ መሆናቸውን በወላይታ ዞን የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች ተናገሩ