ክርስቲያኖ ሮናልዶ የክብር ሽልማት ተሰጠው
ፖርቹጋላዊው ኮከብ ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች በመባል የክብር ሽልማት ተሰጥቶታል።
የአምስት ጊዜ የባሎንዲኦር አሸናፊው ሮናልዶ ይህ የክብር ሽልማት የተሰጠው ከፖርቹጋል እግርኳስ ፌዴሬሽን ነው።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከሽልማቱ በኋላ በሰጠው አስተያየት በርካታ ሽልማቶች ያሉት ቢሆንም ይሄኛው ሽልማት ግን የተለየ መሆኑን ተናግሯል።
የ40 ዓመቱ ተጫዋች ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን እስካሁን በ223 ጨዋታዎች 141 ጎሎችን በማስቆጠር በመላው ዓለም በብሔራዊ ደረጃ የምንጊዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ መሆኑ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽንስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
አካል ጉዳተኝነት ውጤታማ ከመሆን ያልገደባቸው አቶ ሀብታሙ ለማ
የፈተና አስተዳደር ሥርዓትን በማዘመን ኩረጃን በማስቀረት የተሻሉ ተማሪዎችን ማፍራት እየተቻለ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ