ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ውሉን ለማራዘም ተስማማ
ሀዋሳ፡ መስከረም 15/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ፈረንሳዊው የመሐል ስፍራ ተከላካይ በአርሰናል ውሉን ለተጨማሪ ዓመት ለማራዘም ከስምምነት ላይ መድረሱ ተገለጸ።
የ24 ዓመቱ ተጫዋች በመድፈኞቹ ቤት የረዥም ዓመት ውል ለመፋራረም መስማማቱ ነው የተገለጸው።
አሁን ላይ በሰሜን ለንደኑ ክለብ ያለው ውል ሊጠናቀቅ ከሁለት ዓመት ያነሰ ጊዜ የቀረው ሳሊባ በሪያል ማድሪድ በጥብቅ የሚፈለግ ተጫዋች ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ሆኖም ዊሊያም ሳሊባ በአርሰናል ቤት በተጫዋችነት ለመቀጠል ፋቃደኛ መሆኑን የ ዘ አትሌቲክ መረጃ ያስረዳል።
አርሰናልም በሚቀጥሉት ቀናት ወሳኝ ተከላካዩ ውሉን ማራዘሙን ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ አውሮፓውያኑ በ2019 ከሀገሩ ክለብ ሴንት ኤቲኤን ለአርሰናል የፈረመው ሳሊባ ውሉን የሚያራዝም ከሆነ በዚህ ዓመት ለአርሰናል ኮንትራቱን ያራዘመ አምስተኛው ተጫዋች ይሆናል።
በቅርቡ አጣማሪው ጋብርኤል ማጋሌሽ፣ ኤታን ዋኔሪ፣ ሌዊስ ስኬሊ እና ሊያንድሮ ትሮሳርድ በአርሰናል ለመቆየት ውላቸውን ማደሳቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የፕሪሚዬር ሊጉ የመክፈቻ ሳምንታት ጨዋታዎች በሀዋሳ እንደሚካሄዱ ተገለፀ
ብሩኖ ፈርናንዴዝ ወደ ሳውዲ ፕሮ ሊግ የማቅናት ፍላጎት እንደሌለው ተገለፀ
የሰርከስ ስፖርት ሳይንሳዊ ጥበቡን ጠብቆ ለማጎልበት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ