ከደም ተዋፅኦ መድኃኒት በማምረት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገቡ የደም መድኃኒቶችን ለማምረት እየተሰራ ይገኛል – የኢትዮጵያ ደምና ኅብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት
ከደም ተዋፅኦ መድኃኒት በማምረት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገቡ የደም መድኃኒቶችን ለማምረት እየተሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ደምና ኅብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የበጎ ፍቃድ ደም ለጋሾች እና ተቋማት የምስጋና እና የዕውቅና መርሀ ግብር በወላይታ ሶዶ ተከናውኗል፡፡
የብሄራዊ ደም ባንክ ደምና ህብረ ህዋስ ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ጤናዬ ደስታ እንዳሉት፤ የሚቀዳ ደም ጥራቱና ደህንነቱ እንዲረጋገጥ የደም መመርመሪያ ማሽን አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት የመመርመርያ ማሽን የሟሟላት ስራ ይሰራል።
ቋሚ ደም ለጋሾች ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል ያሉት ዳይሬክተሯ፤ አንድ ሰው አንዴ ከለገሰ የ4 ሰዎችን ህይወት ስለሚታደግ ሁሉም አካላት በተነሳሽነት መንፈስ ደም መለገስ እንዳለበትም አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ በክልሉ ደም ከመለገስ አንፃር ለውጦች ቢኖሩም ባህል ከማድረግ አንፃር ክፍተቶች መኖራቸውን አውስተው፤ ቋሚ ለጋሾችን ከማፍራት አንፃርም በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አብራርተዋል።
አክለውም የክትትልና የድጋፍ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን በማስፈን በደም መፍሰስ ምክንያት የሚሞቱ ወገኖችን ህይወት ለመታደግ የደም ባንኮችን የመደገፍ ስራ በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢተው ባለፉት ጊዜያት በክልሉ ደም ለመለገስ የተደረገው ቁርጠኛ እንቅስቃሴ ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለው፤ በቀጣይም ዋጋው ውድ የሆነውን ደም በሚፈለገው ልክ ለማሰባሰብ መስራት ያሻል ሲሉ ጠቁመዋል።
በደም እጦት ህይወታቸውን እያጡ የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመታደግ በቅንጅት መስራት ያሻል ያሉት ወ/ሮ ወላይቴ፤ እንደህዝብ ተወካይነታችን በቀጣይ ውጤት የሚያመጡ የቁጥጥር፣ ክትትልና የድጋፍ ስራዎችን እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል።
በመርሀ ግብሩ የበጎ ፍቃድ ደም ለጋሽ ተቋማት፣ ማህበራት እና ትምህርት ቤቶች ምስጋና እና ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
ዜጎች የራሳቸውን ጤና ማምረት እንዲችሉ የጤና ማጎልበትና የበሽታ መከላከል ሥራ ላይ የሚዲያ ተግባር ላቅ ያለ መሆኑ ተገለጸ
ጉዳት የሚያስከትሉ ተላላፊ በሽታዎችን ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት በተከታታይነት መከላከል እንደሚጠበቅባቸው ኢንስቲትዩቱ አሳሰበ
ትኩረት የሚሹ ሓሩራማ በሽታዎችን በዘላቂነት ለመከላከል የአካባቢ ጤና አጠባበቅ ስራን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ