በቴክኖሎጂ የታገዘ መንግሥት የግዥ ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ የሀብት ብክነትን መቀነስ ይገባል – ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
የኢፌዲሪ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን በመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥረዓት አተገባበር ዙሪያ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቦንጋ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ በቴክኖሎጂ የታገዘ መንግሥት የግዥ ስርዓት ተግባራዊ በማድረግ የሀብት ብክነትን መቀነስ ይገባል ብለዋል።
የኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት ውስን የኾነውን የህዝብና የመንግሥት ሀብት በተገቢው ከማስተዳደር ባለፈው በግዥ ስርዓት ሂደት ውስጥ ፍትሀዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ስረዓት እንደሆነ ገልጸዋል።
በክልሉ የሚከናወኑ የመንግሥት የንብረትና የአግልግሎት ግዥዎችን በቴክኖሎጂ በተጋዘ መልኩ በማሳለጥ የጊዜና የሀብት ብክነትን ለመቀነስ የክልሉ መንግሥት በቁርጠኝነት አንደሚሰራም ርዕሰ መስተዳድሩ የገለጹት።
በመድረኩ የተገኙት የኢፌዴሪ የግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ የመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት (ኢጂፒ) አስፈላጊነትና ጠቀሜታዎች እንዲሁም ዝርዝር አፈጻጸም ዙሪያ ገለጻ እየሰጡ ይገኛል።
ምንጭ፡ የክልሉ መንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

More Stories
የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ በመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሰኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አሰታወቀ
ሳውላ ከተማን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ የማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተካሄደ ነው
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪዝም ሀብቶችን በማልማትና ሰላምን በማጽናት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል