በዳውሮ ዞን በሎማ ቦሣ ወረዳ የወባ ወረርሽን ለመከላከል የኬሚካል ርጭት እየተካደ ነው
የወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ብርሃኑ ድግሦ በወረዳወ በሚገኙ 27 ቀበሌያት መከላከልን መሠረት ያደረገ የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ እያንዳንዱ ነዋሪ ንጽሁ ሽንት ቤትን እንዲኖረው በማድረግ ፣ደርቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ በአግባቡ የማስወገድ ሥራ ስርዓት እንዲኖር ማድረግ መቻሉን ገልጿል።
በወባ ትንኝ መራቢያ አከባቢዎች የቤት ለቤት ኬሚካል ርጭት ከማስመጀመር ባለፈ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ ሥራዎች መከናወኑን አስረድተዋል። ኬሚካል ርጭት የወባ በሽታ ወረርሽኝ ከፍተኛ በሆነባቸው በ12 ቀበሌያት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡
ህብረተሰቡም ለተከታታይ 6 ወራት ኬሚካል በተረጨ ቤት ላይ ቀለም ይሁን ተመሳሳይ ነገር ባለመቀባት እንዲሁም አጎበር በተገቢው በመጠቀም የውሃ ማፋሰሻዎች በመስራት ራሳቸውን ከወረርሽኙ መጠበቅ እንደሚገባም አመላክተዋል።
አዘጋጅ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አስታወቀ
በኮሬ ዞን አራተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በይፈ ተጀመረ
የጡት ካንሰር ተገቢው ህክምና በወቅቱ ካልተደረገ ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ እንደመሆኑ ድንገት ሲያጋጥም በባህል ህክምና ከመዘናጋት ይልቅ በአፋጠኝ ወደ ጤና ተቋማት መሄድ ተገቢ ነው – ዶክተር ተሾመ አለምቦ