በዳውሮ ዞን በሎማ ቦሣ ወረዳ የወባ ወረርሽን ለመከላከል የኬሚካል ርጭት እየተካደ ነው
የወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ብርሃኑ ድግሦ በወረዳወ በሚገኙ 27 ቀበሌያት መከላከልን መሠረት ያደረገ የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ እያንዳንዱ ነዋሪ ንጽሁ ሽንት ቤትን እንዲኖረው በማድረግ ፣ደርቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ በአግባቡ የማስወገድ ሥራ ስርዓት እንዲኖር ማድረግ መቻሉን ገልጿል።
በወባ ትንኝ መራቢያ አከባቢዎች የቤት ለቤት ኬሚካል ርጭት ከማስመጀመር ባለፈ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ ሥራዎች መከናወኑን አስረድተዋል። ኬሚካል ርጭት የወባ በሽታ ወረርሽኝ ከፍተኛ በሆነባቸው በ12 ቀበሌያት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡
ህብረተሰቡም ለተከታታይ 6 ወራት ኬሚካል በተረጨ ቤት ላይ ቀለም ይሁን ተመሳሳይ ነገር ባለመቀባት እንዲሁም አጎበር በተገቢው በመጠቀም የውሃ ማፋሰሻዎች በመስራት ራሳቸውን ከወረርሽኙ መጠበቅ እንደሚገባም አመላክተዋል።
አዘጋጅ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የወባ ቅድመ መከላከል ስራ ውጤት እያስገኘ መምጣቱን በካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች ተናገሩ
በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል ድጋፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ሩዝ ያመረቱ አርሶ አደሮች ምርታማ መሆናቸውን ገለፁ
በክልሉ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ እናቶችና ሴቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናቸው እንዲጠበቅ በትኩረት መሠራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ