በዳውሮ ዞን በሎማ ቦሣ ወረዳ የወባ ወረርሽን ለመከላከል የኬሚካል ርጭት እየተካደ ነው
የወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ብርሃኑ ድግሦ በወረዳወ በሚገኙ 27 ቀበሌያት መከላከልን መሠረት ያደረገ የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ እያንዳንዱ ነዋሪ ንጽሁ ሽንት ቤትን እንዲኖረው በማድረግ ፣ደርቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ በአግባቡ የማስወገድ ሥራ ስርዓት እንዲኖር ማድረግ መቻሉን ገልጿል።
በወባ ትንኝ መራቢያ አከባቢዎች የቤት ለቤት ኬሚካል ርጭት ከማስመጀመር ባለፈ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ ሥራዎች መከናወኑን አስረድተዋል። ኬሚካል ርጭት የወባ በሽታ ወረርሽኝ ከፍተኛ በሆነባቸው በ12 ቀበሌያት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡
ህብረተሰቡም ለተከታታይ 6 ወራት ኬሚካል በተረጨ ቤት ላይ ቀለም ይሁን ተመሳሳይ ነገር ባለመቀባት እንዲሁም አጎበር በተገቢው በመጠቀም የውሃ ማፋሰሻዎች በመስራት ራሳቸውን ከወረርሽኙ መጠበቅ እንደሚገባም አመላክተዋል።
አዘጋጅ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
ህብረተሰቡ በሽታን ለመከላከል የሚሰጡ ክትባቶችን በአግባቡ በመውሰድ እንዳለበት ተገለጸ
የመስቀል በዓል አከባበር ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው የማይዳሰሱ ቅርሶች መካከል አንዱ ነው
የአርባምንጭ የድል ፋና የመጀሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አንዳንድ በሆስፒታሉ ያገኘናቸዉ ተገልጋዮች ተናገሩ