ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን አስፈረመ
የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን አሳውቋል።
ስፔናዊው የግራ መስመር ተከላካይ በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን የ6 ዓመት ውል ፈርሟል።
ሎስብላንኮዎቹ ከላማሲያ አካዳሚ ለተገኘው ተጫዋች 60 ሚሊዮን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ መክፈላቸው ተገልጿል።
ማርክ ኩኩሬላ በ2022 ከብራይተን ነበር ቼልሲን የተቀላቀለው።
በምዕራብ ለንደኑ ክለብ በነበረው የአራት ዓመታት ቆይታው 150 ጨዋታዎችን ተሰልፎ አከናውኗል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሪያል ማድሪድ ያን ዲዮማንዴን በታሪካዊ የዝውውር ክፍያ አስፈረመ
ብሩኖ ጊማሬስ የሕክምና ምርመራውን በስኬት አጠናቀቀ
9 ክለቦች በአዲስ አሰልጣኞች ፍልሚያቸውን የሚጀምሩበት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ