የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ
ሀዋሳ: መጋቢት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሚቀጥሉት ሶስት ወራት የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
በክልሉ የቀጣይ የ90 ቀናት የመንግስትና የፓርቲ የስራ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
ከመጋቢት 1 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም በመንግስትና በፓርቲ መሳካት አለባቸው ተብለው የታለሙ ዕቅዶችን ወደ መሬት ማውረድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እተወያዩ ያሉት።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ዕቅዱ አላማው እንዲያሳካ አመራሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን መከታተል ይኖርበታል ብለዋል።
ባለፋት ጊዜያት ፈተናዎችን በመቋቋም ውጤት እንደመጣው ሁሉ ዕቅዱን አሳክቶ የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ አንድነት ላይ ቆሞ መስራት ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ የልማት ዘርፍ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱን የዳዉሮ ዞን ግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ልማት መምሪያ አስታወቀ