የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ
ሀዋሳ: መጋቢት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሚቀጥሉት ሶስት ወራት የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
በክልሉ የቀጣይ የ90 ቀናት የመንግስትና የፓርቲ የስራ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
ከመጋቢት 1 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም በመንግስትና በፓርቲ መሳካት አለባቸው ተብለው የታለሙ ዕቅዶችን ወደ መሬት ማውረድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እተወያዩ ያሉት።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ዕቅዱ አላማው እንዲያሳካ አመራሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን መከታተል ይኖርበታል ብለዋል።
ባለፋት ጊዜያት ፈተናዎችን በመቋቋም ውጤት እንደመጣው ሁሉ ዕቅዱን አሳክቶ የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ አንድነት ላይ ቆሞ መስራት ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ