የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ ተገለጸ
ሀዋሳ: መጋቢት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሚቀጥሉት ሶስት ወራት የማህበረሰቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ አስቻይ የሆኑ ስራዎች ላይ ማተኮር ከአመራሩ እንደሚጠበቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
በክልሉ የቀጣይ የ90 ቀናት የመንግስትና የፓርቲ የስራ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።
ከመጋቢት 1 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም በመንግስትና በፓርቲ መሳካት አለባቸው ተብለው የታለሙ ዕቅዶችን ወደ መሬት ማውረድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እተወያዩ ያሉት።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ዕቅዱ አላማው እንዲያሳካ አመራሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን መከታተል ይኖርበታል ብለዋል።
ባለፋት ጊዜያት ፈተናዎችን በመቋቋም ውጤት እንደመጣው ሁሉ ዕቅዱን አሳክቶ የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ አንድነት ላይ ቆሞ መስራት ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ