በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢሠራ ወረዳ ተገልጋዮች ተናገሩ
የወረዳው አስተዳደር በበኩሉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
በኢሠራ ወረዳ ባሌ ጤና ጣቢያ ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ሲሆኑ በአገልግሎቱ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና አገልግሎት ከተጀመረበት አንስተው አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመው በተመዘገቡት የአባልነት ካርድ ሙሉ ቤተሰብ እየታከመ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በመድኃኒት እጥረትና አገልግሎት አስጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች እንደፈቱ ጠይቀዋል፡፡
የባሌ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ስራአስኪያጅ የሆኑት አቶ አለምሰግድ መኩሪያ በበኩላቸው የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ዙሪያ ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ስራ ለመስራት እስከ ቀበሌ የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በርካታ አዲስ አባላትን በማስመዝገብ እና ለነባሮቹ እድሳት በማድረግ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማሳለጥ በመስራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ በየነ በበጀት ዓመቱ 8ሺህ 52 የህብረተሰብ ክፍሎችን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅደው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ተክሌ ከማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት እና የአባላት ምዝገባ እንዲሁም የካርድ እድሳት ስራ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ የወረዳው ባለድርሻ አካላትን በየቀበሌው መድበው ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል
አዘጋጅ፦ አፈወርቅ ኦሹ ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የተከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ ተደረገ
ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ በአርባ ምንጭ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 132 ተማሪዎችን አስመረቀ
በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ