በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢሠራ ወረዳ ተገልጋዮች ተናገሩ
የወረዳው አስተዳደር በበኩሉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።
በኢሠራ ወረዳ ባሌ ጤና ጣቢያ ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት ሲሆኑ በአገልግሎቱ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና አገልግሎት ከተጀመረበት አንስተው አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመው በተመዘገቡት የአባልነት ካርድ ሙሉ ቤተሰብ እየታከመ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በመድኃኒት እጥረትና አገልግሎት አስጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች እንደፈቱ ጠይቀዋል፡፡
የባሌ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ስራአስኪያጅ የሆኑት አቶ አለምሰግድ መኩሪያ በበኩላቸው የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ዙሪያ ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ስራ ለመስራት እስከ ቀበሌ የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በርካታ አዲስ አባላትን በማስመዝገብ እና ለነባሮቹ እድሳት በማድረግ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማሳለጥ በመስራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ በየነ በበጀት ዓመቱ 8ሺህ 52 የህብረተሰብ ክፍሎችን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅደው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ተክሌ ከማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት እና የአባላት ምዝገባ እንዲሁም የካርድ እድሳት ስራ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ የወረዳው ባለድርሻ አካላትን በየቀበሌው መድበው ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል
አዘጋጅ፦ አፈወርቅ ኦሹ ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ