የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 24ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ በጉባኤው መክፈቻ እንዳሉት፤ በዞኑ በሁሉም መስኮች በ2017 የመጀመሪያ 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል።
የዞኑ አስተዳደር ምክር የ6 ወር አፈጻጻም ሪፖርት ቀርቦ ከምክር ቤቱ አባላት በመሠረተ ልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እየተነሱ ነው።
በምክር ቤቱ የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት የሚቀርብ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችም ለምክር ቤቱ ቀርበው ይፀጽቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: የአለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በክራምት ወራት ሲከውኑት የነበረውን የበጎ ተግባር በበጋ ወራት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በስልጤ ዞን የሁልባረግ ወረዳ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተናገሩ
ጥራት ያለውን ትምህርት ለዜጎች ለማድረስ እየተጉ ያሉትን ባለድርሻዎች ማበረታታት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለፀ
በሀገር በቀል ዕውቀት የሚታወቀውን የአካባቢውን እምቅ አቅም አጉልቶ በማሳየት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ዕድገት ማፋጠን እንደሚገባ ተገለፀ