የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 24ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ በጉባኤው መክፈቻ እንዳሉት፤ በዞኑ በሁሉም መስኮች በ2017 የመጀመሪያ 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል።
የዞኑ አስተዳደር ምክር የ6 ወር አፈጻጻም ሪፖርት ቀርቦ ከምክር ቤቱ አባላት በመሠረተ ልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እየተነሱ ነው።
በምክር ቤቱ የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት የሚቀርብ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችም ለምክር ቤቱ ቀርበው ይፀጽቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: የአለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ