የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 24ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ በጉባኤው መክፈቻ እንዳሉት፤ በዞኑ በሁሉም መስኮች በ2017 የመጀመሪያ 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል።
የዞኑ አስተዳደር ምክር የ6 ወር አፈጻጻም ሪፖርት ቀርቦ ከምክር ቤቱ አባላት በመሠረተ ልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እየተነሱ ነው።
በምክር ቤቱ የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት የሚቀርብ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችም ለምክር ቤቱ ቀርበው ይፀጽቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: የአለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ