የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 24ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ በጉባኤው መክፈቻ እንዳሉት፤ በዞኑ በሁሉም መስኮች በ2017 የመጀመሪያ 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል።
የዞኑ አስተዳደር ምክር የ6 ወር አፈጻጻም ሪፖርት ቀርቦ ከምክር ቤቱ አባላት በመሠረተ ልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ጥያቄዎችና አስተያየቶች እየተነሱ ነው።
በምክር ቤቱ የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት የሚቀርብ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችም ለምክር ቤቱ ቀርበው ይፀጽቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: የአለቃል ደስታ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ