ሂጂራ ባንክ ሚዛን አማን ቅርንጫፍ ታላቁን የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ በሚዛን አማን ከተማ በሚገኘው አዝሃር መስጂድ በመገኘት በከተማዋ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የኢፍጣር ድጋፎች አድርጓል።
ባንኩ በዕለቱ 75 ለሚሆኑና ለችግር ለተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከ100 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ ዱቄትና ዘይት ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል።
በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንትና የነስር መስጅድ ኢማም ሼህ አደም መሀመድ፤ ሂጅራ ባንክ የእስላማዊ አስተምህሮቶችን በመተግበር ለችግር የተጋሉጡትን ወገኖች መርዳቱ የሚያስመሰግነው መልካም ስራ መሆኑን ገልጸው በሌሎች ተቋማትም ጅምሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በረመዳን ጾም ወር እንዲህ ዓይነት መረዳዳትና ችግረኞችን መደገፍ የእምነቱ አስተምህሮ እና ተግባር በመሆኑ የሚያስደስት ነው ብለዋል።
በሚዛን አማን ከተማ የሚገኘው የአዝሀር መስጅድ ኢማም ሸህ መሀመድ ፈትህ እንደገለፁት፤ በእስልምና ሀይማኖት አስተምህሮ ከተቀመጡት መሰረታዊ ነጥቦች የረመዳንን ፆም መጾም፣ የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍና መንከባከብ እንዲሁም ዘካን በአግባቡ ማውጣት ተጠቃሾች ናቸው።
የሂጅራ ባንክ የደቡብ ምዕራብ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ መሀመድ በበኩላቸው፤ ባንኩ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ለሙስሊሙ ሕብረተሰብ የሚሰጥ ሲሆን እንደሀገር በተለያዩ አካባቢዎች ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችንና አቅመ ደካሞችን እየደገፈ እንዳለ ገልጸዋል።
ባንኩ 1446ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ በሚዛን አማን ከተማ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖች ድጋፍ ማድረጋቸውን አስረድተዋል።
ድጋፉ 75 ለሚሆኑና ለችግር ለተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከ100 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ ዱቄና ዘይት ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀው በቀጣይም ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል
በስነ ስርዓቱ ላይ የሀይማኖት መሪዎች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የሂጅራ ባንክ አመራርና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል