የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ ቤተ መንግስት ህንፃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ
ክልሉ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመስሪያ ቤት እጥረት ማጋጠሙን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ አዲሱ ፕሮጀክት ክልሉን ከከፍተኛ ወጪ ይታደጋል ብለዋል፡፡
በክልሉ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ከሚኖራቸው ውበትና ምቹ የስራ ቦታነት ባሻገር የሚፈጥሩት የስራ ዕድል እንደሚኖር ነው ዶ/ር እንደሻው በዚሁ ወቅት ያነሱት፡፡
የዛሬው የመሰረት ድንጋይ የማኖር መርሃ ግብር በክልሉ ሰባት ማዕከላት በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ለተመሳሳይ የህንፃ ግንባታ ማስጀመሪያ ነው። የውስጥ ስራውን ሲጨምር እስከ 7 ቢሊየን ብር ይጠይቃል ነው የተባለው፡፡
የሃድያ ዞን አስተዳዳሪ ማቴዎስ አንዮ መሠል መሰረተ ልማት በአካባቢው መገንባቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታን ያስገኛል ብለዋል።
በሆሳና ከተማ የሚገነባው ቤተ መንግስት እና መሰብሰቢያ አዳራሽን በዋናነት ያካተተ ስለመሆኑ ግንባታውን የወሰደው ተቋራጭ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዳንኤል ብርሃኑ ገልጸዋል።
ስራው በስድስት ወራት ጊዜ ቀንና ሌሊት ተሰርቶ ይጠናቀቃል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ