የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ ቤተ መንግስት ህንፃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ
ክልሉ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመስሪያ ቤት እጥረት ማጋጠሙን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ አዲሱ ፕሮጀክት ክልሉን ከከፍተኛ ወጪ ይታደጋል ብለዋል፡፡
በክልሉ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ከሚኖራቸው ውበትና ምቹ የስራ ቦታነት ባሻገር የሚፈጥሩት የስራ ዕድል እንደሚኖር ነው ዶ/ር እንደሻው በዚሁ ወቅት ያነሱት፡፡
የዛሬው የመሰረት ድንጋይ የማኖር መርሃ ግብር በክልሉ ሰባት ማዕከላት በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ለተመሳሳይ የህንፃ ግንባታ ማስጀመሪያ ነው። የውስጥ ስራውን ሲጨምር እስከ 7 ቢሊየን ብር ይጠይቃል ነው የተባለው፡፡
የሃድያ ዞን አስተዳዳሪ ማቴዎስ አንዮ መሠል መሰረተ ልማት በአካባቢው መገንባቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታን ያስገኛል ብለዋል።
በሆሳና ከተማ የሚገነባው ቤተ መንግስት እና መሰብሰቢያ አዳራሽን በዋናነት ያካተተ ስለመሆኑ ግንባታውን የወሰደው ተቋራጭ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዳንኤል ብርሃኑ ገልጸዋል።
ስራው በስድስት ወራት ጊዜ ቀንና ሌሊት ተሰርቶ ይጠናቀቃል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል