የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ ቤተ መንግስት ህንፃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ
ክልሉ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመስሪያ ቤት እጥረት ማጋጠሙን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ አዲሱ ፕሮጀክት ክልሉን ከከፍተኛ ወጪ ይታደጋል ብለዋል፡፡
በክልሉ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ከሚኖራቸው ውበትና ምቹ የስራ ቦታነት ባሻገር የሚፈጥሩት የስራ ዕድል እንደሚኖር ነው ዶ/ር እንደሻው በዚሁ ወቅት ያነሱት፡፡
የዛሬው የመሰረት ድንጋይ የማኖር መርሃ ግብር በክልሉ ሰባት ማዕከላት በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ለተመሳሳይ የህንፃ ግንባታ ማስጀመሪያ ነው። የውስጥ ስራውን ሲጨምር እስከ 7 ቢሊየን ብር ይጠይቃል ነው የተባለው፡፡
የሃድያ ዞን አስተዳዳሪ ማቴዎስ አንዮ መሠል መሰረተ ልማት በአካባቢው መገንባቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታን ያስገኛል ብለዋል።
በሆሳና ከተማ የሚገነባው ቤተ መንግስት እና መሰብሰቢያ አዳራሽን በዋናነት ያካተተ ስለመሆኑ ግንባታውን የወሰደው ተቋራጭ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዳንኤል ብርሃኑ ገልጸዋል።
ስራው በስድስት ወራት ጊዜ ቀንና ሌሊት ተሰርቶ ይጠናቀቃል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ