የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ ቤተ መንግስት ህንፃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ
ክልሉ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመስሪያ ቤት እጥረት ማጋጠሙን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ አዲሱ ፕሮጀክት ክልሉን ከከፍተኛ ወጪ ይታደጋል ብለዋል፡፡
በክልሉ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ከሚኖራቸው ውበትና ምቹ የስራ ቦታነት ባሻገር የሚፈጥሩት የስራ ዕድል እንደሚኖር ነው ዶ/ር እንደሻው በዚሁ ወቅት ያነሱት፡፡
የዛሬው የመሰረት ድንጋይ የማኖር መርሃ ግብር በክልሉ ሰባት ማዕከላት በ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ለተመሳሳይ የህንፃ ግንባታ ማስጀመሪያ ነው። የውስጥ ስራውን ሲጨምር እስከ 7 ቢሊየን ብር ይጠይቃል ነው የተባለው፡፡
የሃድያ ዞን አስተዳዳሪ ማቴዎስ አንዮ መሠል መሰረተ ልማት በአካባቢው መገንባቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታን ያስገኛል ብለዋል።
በሆሳና ከተማ የሚገነባው ቤተ መንግስት እና መሰብሰቢያ አዳራሽን በዋናነት ያካተተ ስለመሆኑ ግንባታውን የወሰደው ተቋራጭ ምክትል ስራ አስኪያጅ ዳንኤል ብርሃኑ ገልጸዋል።
ስራው በስድስት ወራት ጊዜ ቀንና ሌሊት ተሰርቶ ይጠናቀቃል ተብሏል።
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ