የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ።
ቢሮ በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ተግባራት ዙሪያ ከቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ቦንጋ ከተማ ምክክር አካሂዷል።
በቢሮው የጸጥታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊና የወሳኝ ኩነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ደነቀ በተለያዩ አካባቢዎች የምዝገባ ስርዓቱ ያለበትን ደረጃ ለመገምገምና በምዝገባ ወቅት የሚፈጠሩ ክፍቶችን በአፋጣኝ ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል።
በዚህም በክልሉ ባሉ 6 ዞኖች የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ኃላፊው አንስተዋል።
የምዝገባ ስርዓቱ እንዲሳለጥ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በምክክር መድረኩ በ6 ዞኖች የተደረጉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ግብረ መልስ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በክልሉ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ዘርፍ መረጃ ቅበላ አቅርቦት አሪካይቭንግ ዳይሬክትሬት ዳይሬክተር አቶ በረከት መላኩ በበኩላቸው፥ የታዩ መልካም ልምዶችን ማጠናከርና ክፍቶች ላይ በቀጣይ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት የምዝገባ ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።
ዘጋቢ፡ መቅደስ ታደሠ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል