የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ የካቲት 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ።
ቢሮ በወሳኝ ኩነት ምዝገባ ተግባራት ዙሪያ ከቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ቦንጋ ከተማ ምክክር አካሂዷል።
በቢሮው የጸጥታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊና የወሳኝ ኩነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ደነቀ በተለያዩ አካባቢዎች የምዝገባ ስርዓቱ ያለበትን ደረጃ ለመገምገምና በምዝገባ ወቅት የሚፈጠሩ ክፍቶችን በአፋጣኝ ለመቅረፍ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል።
በዚህም በክልሉ ባሉ 6 ዞኖች የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ኃላፊው አንስተዋል።
የምዝገባ ስርዓቱ እንዲሳለጥ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በምክክር መድረኩ በ6 ዞኖች የተደረጉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ግብረ መልስ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በክልሉ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ዘርፍ መረጃ ቅበላ አቅርቦት አሪካይቭንግ ዳይሬክትሬት ዳይሬክተር አቶ በረከት መላኩ በበኩላቸው፥ የታዩ መልካም ልምዶችን ማጠናከርና ክፍቶች ላይ በቀጣይ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት የምዝገባ ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን በባለቤትነት ስሜት እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።
ዘጋቢ፡ መቅደስ ታደሠ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ