የቤንች ሸኮ ዞን አጠቃላይ የትምህርት አመራሮች የዞኑ የትምህርት ስራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።
በውይይቱ መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደግፌ ኩድን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትምህርት ተሳትፎና ጥራት ላይ እየታየ የመጣውን ክፍተት ማረም ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ሥራ በርካታ ባለድርሻ አካላት ያሉት በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ በማስተባበርና በማቀናጀት የትምህርት አመራሩ በሚገባ መምራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት፤ በትምህርት ተሳትፎ፣ ብክነትና በአጠቃላይ የትምህርት ስራ ላይ የሚታየውን የትምህርት ስብራት ለማረም ወሳኝ ወቅት ላይ ስለምንገኝ ርብርብ ይጠይቃል።
የመምሪያው ሀላፊ የሴክተሩን የእስካሁን እቅድ አፈፃፀም እና የመወያያ መነሻ ሀሳብ ሰነድ ለታዳሚያን ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም በተነሱት ጉዳዮች ላይ በመወያየት ላይ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ወዳጆ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ