የቤንች ሸኮ ዞን አጠቃላይ የትምህርት አመራሮች የዞኑ የትምህርት ስራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።
በውይይቱ መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደግፌ ኩድን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትምህርት ተሳትፎና ጥራት ላይ እየታየ የመጣውን ክፍተት ማረም ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ሥራ በርካታ ባለድርሻ አካላት ያሉት በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ በማስተባበርና በማቀናጀት የትምህርት አመራሩ በሚገባ መምራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት፤ በትምህርት ተሳትፎ፣ ብክነትና በአጠቃላይ የትምህርት ስራ ላይ የሚታየውን የትምህርት ስብራት ለማረም ወሳኝ ወቅት ላይ ስለምንገኝ ርብርብ ይጠይቃል።
የመምሪያው ሀላፊ የሴክተሩን የእስካሁን እቅድ አፈፃፀም እና የመወያያ መነሻ ሀሳብ ሰነድ ለታዳሚያን ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም በተነሱት ጉዳዮች ላይ በመወያየት ላይ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ወዳጆ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል