የቤንች ሸኮ ዞን አጠቃላይ የትምህርት አመራሮች የዞኑ የትምህርት ስራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።
በውይይቱ መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደግፌ ኩድን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትምህርት ተሳትፎና ጥራት ላይ እየታየ የመጣውን ክፍተት ማረም ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ሥራ በርካታ ባለድርሻ አካላት ያሉት በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ በማስተባበርና በማቀናጀት የትምህርት አመራሩ በሚገባ መምራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት፤ በትምህርት ተሳትፎ፣ ብክነትና በአጠቃላይ የትምህርት ስራ ላይ የሚታየውን የትምህርት ስብራት ለማረም ወሳኝ ወቅት ላይ ስለምንገኝ ርብርብ ይጠይቃል።
የመምሪያው ሀላፊ የሴክተሩን የእስካሁን እቅድ አፈፃፀም እና የመወያያ መነሻ ሀሳብ ሰነድ ለታዳሚያን ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም በተነሱት ጉዳዮች ላይ በመወያየት ላይ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ወዳጆ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ