የቤንች ሸኮ ዞን አጠቃላይ የትምህርት አመራሮች የዞኑ የትምህርት ስራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።
በውይይቱ መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደግፌ ኩድን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትምህርት ተሳትፎና ጥራት ላይ እየታየ የመጣውን ክፍተት ማረም ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ሥራ በርካታ ባለድርሻ አካላት ያሉት በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ በማስተባበርና በማቀናጀት የትምህርት አመራሩ በሚገባ መምራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት፤ በትምህርት ተሳትፎ፣ ብክነትና በአጠቃላይ የትምህርት ስራ ላይ የሚታየውን የትምህርት ስብራት ለማረም ወሳኝ ወቅት ላይ ስለምንገኝ ርብርብ ይጠይቃል።
የመምሪያው ሀላፊ የሴክተሩን የእስካሁን እቅድ አፈፃፀም እና የመወያያ መነሻ ሀሳብ ሰነድ ለታዳሚያን ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም በተነሱት ጉዳዮች ላይ በመወያየት ላይ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ወዳጆ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በኮሬ ዞን የአስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች መልሶ የማደራጀት ምክክር መድረክ ተካሄደ
በአጋር ድርጅቶች የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች የመንግስት የልማት ክፍተት በመሙላት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በሌማት ትሩፋት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን የምዕራብ አባያ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ