በድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥርዓት ላይ የጤና ልማት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ የካቲት 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥርዓት ጀምሮ በኢንስቲትዩቱ ያሉ ተያያዥ የጤና ልማት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ እና በኢንስቲትዩቱ የሥርዓተ-ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማስረሻ ተሰማ የተመራ ሉዑክ ጂንካ ከተማ ተገኝተው በኢንስቲትዩቱ ከቢሮ አደረጃጀት ጀምሮ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝትና ውይይት አድርገዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ በንግግራቸው የጉብኝቱ ዋና አላማ ከድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥርዓት ጀምሮ ያሉ የጥናትና ምርምር፣ የመረጃ ሥርዓትና በክልሉ አርባምንጭ እና ጂንካ ላይ እየተገነቡ ያሉ የላብራቶሪ ማዕከላት ያሉበት የግንባታ ደረጃ ጉብኝት በማድረግ በአጠቃላይ በኢንስቲትዩቱ የሚሰሩ የጤና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ እና በኢንስቲትዩቱ የሥርዓተ-ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማስረሻ ተሰማ በጋራ እንደገለፁት ለጥናትና ምርምር ሥራ ከሰው ኃይል ጀምሮ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ለማሰልጠንና በተለያዩ ጉዳዮች በቅንጅት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በተቋሙ ያሉ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት ውጤታማ ተግባራት ማከናወን የሚያስችል መግባባት የተፈጠረበት ውይይት እንደሆነ አመላክተዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል