የምግብ ስርዓትን ለማሻሻል የጥናትና ምርምር ሥራን በማጠናከር ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ ተናገሩ
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዞኖችና ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ የሥነ-ምግብ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች ለ4 ቀን የቆየ ሰልጠና ሰጥቷል።
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሔራዊ የሥነ-ምግብ መረጃ ማዕከል አሰተባባሪ ዶ/ር አረጋሽ ሳሙኤል በንግግራቸው፤ የስልጠናው ዓላማ በየክልሉ ያሉ የጤና ኢንስቲትዩቶችን ማጠናከርና ከሥርዓተ ምግብ አንፃር በክልሉ ያሉ ባህላዊ ምግቦችን በመጠቀም የምግብ ደህንነትን ለማረጋገጥ ግንዛቤ አግኝተው እንዲያሰተዋውቁና የመረጃ ልውውጥ ሥርዓትን በማጠናከር ለውሳኔ ሰጪ አካላት ምቹ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስልጠና መሆኑን አንስተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ በበኩላቸው፤ በሥርዓተ ምግብ ዙሪያ የሚደረጉ ጥናቶች ምርምሮች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል በመሆኑ ስልጠናውን የሰጡ አካላትን አመስግነዋል።
እንደ ሀገር የመቀንጨር አደጋ 41 በመቶ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ፤ ሰልጣኞቹ ባገኙት ግንዛቤ ከሥርዓተ ምግብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በተጨባጭ መረጃ በመያዝ በጥናትና ምርምር በማሻሻል ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ለዚህም ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንደሚያግዝ አመላክተዋል።
ከሰልጣኞች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አሰተያየት በጥናት የተመሰረተ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን በመዘርጋት ትክክለኛ መረጃ በማውጣት ለጥናትና ለፖሊስ አውጪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚያስችል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የተከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ ተደረገ
ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ በአርባ ምንጭ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 132 ተማሪዎችን አስመረቀ
በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ