የምግብ ስርዓትን ለማሻሻል የጥናትና ምርምር ሥራን በማጠናከር ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ ተናገሩ
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዞኖችና ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ የሥነ-ምግብ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች ለ4 ቀን የቆየ ሰልጠና ሰጥቷል።
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሔራዊ የሥነ-ምግብ መረጃ ማዕከል አሰተባባሪ ዶ/ር አረጋሽ ሳሙኤል በንግግራቸው፤ የስልጠናው ዓላማ በየክልሉ ያሉ የጤና ኢንስቲትዩቶችን ማጠናከርና ከሥርዓተ ምግብ አንፃር በክልሉ ያሉ ባህላዊ ምግቦችን በመጠቀም የምግብ ደህንነትን ለማረጋገጥ ግንዛቤ አግኝተው እንዲያሰተዋውቁና የመረጃ ልውውጥ ሥርዓትን በማጠናከር ለውሳኔ ሰጪ አካላት ምቹ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስልጠና መሆኑን አንስተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ በበኩላቸው፤ በሥርዓተ ምግብ ዙሪያ የሚደረጉ ጥናቶች ምርምሮች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል በመሆኑ ስልጠናውን የሰጡ አካላትን አመስግነዋል።
እንደ ሀገር የመቀንጨር አደጋ 41 በመቶ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ፤ ሰልጣኞቹ ባገኙት ግንዛቤ ከሥርዓተ ምግብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በተጨባጭ መረጃ በመያዝ በጥናትና ምርምር በማሻሻል ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ለዚህም ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንደሚያግዝ አመላክተዋል።
ከሰልጣኞች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አሰተያየት በጥናት የተመሰረተ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን በመዘርጋት ትክክለኛ መረጃ በማውጣት ለጥናትና ለፖሊስ አውጪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚያስችል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ