የምግብ ስርዓትን ለማሻሻል የጥናትና ምርምር ሥራን በማጠናከር ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ ተናገሩ
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዞኖችና ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ የሥነ-ምግብ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች ለ4 ቀን የቆየ ሰልጠና ሰጥቷል።
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሔራዊ የሥነ-ምግብ መረጃ ማዕከል አሰተባባሪ ዶ/ር አረጋሽ ሳሙኤል በንግግራቸው፤ የስልጠናው ዓላማ በየክልሉ ያሉ የጤና ኢንስቲትዩቶችን ማጠናከርና ከሥርዓተ ምግብ አንፃር በክልሉ ያሉ ባህላዊ ምግቦችን በመጠቀም የምግብ ደህንነትን ለማረጋገጥ ግንዛቤ አግኝተው እንዲያሰተዋውቁና የመረጃ ልውውጥ ሥርዓትን በማጠናከር ለውሳኔ ሰጪ አካላት ምቹ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስልጠና መሆኑን አንስተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አጉኔ አሾሌ በበኩላቸው፤ በሥርዓተ ምግብ ዙሪያ የሚደረጉ ጥናቶች ምርምሮች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል በመሆኑ ስልጠናውን የሰጡ አካላትን አመስግነዋል።
እንደ ሀገር የመቀንጨር አደጋ 41 በመቶ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ፤ ሰልጣኞቹ ባገኙት ግንዛቤ ከሥርዓተ ምግብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በተጨባጭ መረጃ በመያዝ በጥናትና ምርምር በማሻሻል ለተለያዩ ውሳኔዎች በር እንዲከፍቱ ማስቻል ላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ለዚህም ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንደሚያግዝ አመላክተዋል።
ከሰልጣኞች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አሰተያየት በጥናት የተመሰረተ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን በመዘርጋት ትክክለኛ መረጃ በማውጣት ለጥናትና ለፖሊስ አውጪዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚያስችል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ