የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ የሴቶች ሚና በሚል የውይይት መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው
በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ስራ አስፈፃሚ እና የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ሀላፊ እሌኒ አባይነህ፤ ፓርቲው ባካሄዳቸው መደበኛ ጉባኤዎች ላይ ያሳለፋቸው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች የህዝቡን ሰላምና ልማት በዘላቂነት እንዲረጋገጥ ሴቶች በግንባር ቀደምነት ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ሴቶች በልማት ብቻ ሳይሆን በጦር ሜዳ ላይ ለተቀዳጁት ድል አድዋ ማሳያ ነው የሚሉት ወ/ሮ እሌኒ፤ ሴቶች በሰላሙ ዘርፍም የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ አይተኬ ነው ብለዋል።
የጋሞ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሀኪሜ አየለ በበኩላቸው፤ በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች መተላለፋቸውን ገልፀው ብልፅግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል በማለት ተናግረዋል።
የጋሞ ዞን ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ደመረ፤ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካውና በመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴዎች ውስጥ ሴቶች እንዲሳተፉና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በአደረጃጀት እንዲታቀፉ ፓርቲው በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል።
በመድረኩ በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች እየቀረቡ ሲሆን በቀጣይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ የክልል እና የዞን የፓርቲ ስራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የሴቶች ክንፍ አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል