የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች ለዓድዋ ድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች 129ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አስመልክተው ለኢትዮጵያዊያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የዓድዋ ድል አንድነት እና ብሔራዊ ኩራትን የሚገልጽ ነው ብሏል።
በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለኢትዮጵያ ብልጽግና እና ስኬትን ተመኝቷል።
በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ሁለቱ ሀገራት በታሪክ ጀግንነትን፣ አንድነትን እና ጽናትን የሚጋሩ መሆናቸውን ጠቅሷል።
ሀገራቱ ከታሪኮቻቸው ባሻገር መጪዎቹ ጊዜያት ብሩህ እንደሚሆኑም እምነቱን ገልጿል።
በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያዊያን የጽናት እና የአንድነት ምልክት መሆኑን በመግለጽ፣ ኢትዮጵያዊያን አንድነታቸውን የሚያጠናክሩበት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።
በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የእንግሊዝ፣ የጀርመን እና የኩባን ጨምሮ የተለያዩ ኤምባሲዎች ለበዓሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ