የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች ለዓድዋ ድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች 129ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አስመልክተው ለኢትዮጵያዊያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የዓድዋ ድል አንድነት እና ብሔራዊ ኩራትን የሚገልጽ ነው ብሏል።
በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለኢትዮጵያ ብልጽግና እና ስኬትን ተመኝቷል።
በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ሁለቱ ሀገራት በታሪክ ጀግንነትን፣ አንድነትን እና ጽናትን የሚጋሩ መሆናቸውን ጠቅሷል።
ሀገራቱ ከታሪኮቻቸው ባሻገር መጪዎቹ ጊዜያት ብሩህ እንደሚሆኑም እምነቱን ገልጿል።
በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያዊያን የጽናት እና የአንድነት ምልክት መሆኑን በመግለጽ፣ ኢትዮጵያዊያን አንድነታቸውን የሚያጠናክሩበት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።
በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የእንግሊዝ፣ የጀርመን እና የኩባን ጨምሮ የተለያዩ ኤምባሲዎች ለበዓሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል በሀገር ውስጥ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።
More Stories
የጎፋ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነው
ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ ከተለመደው የመንግስት የስራ ሰዓት ውጭ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ
አባቶቻችን ያስመዘገቡትን ድል ለመድገም የአሁኑ ትውልድ አንድነትን በማጠናከር የተጀመሩ የልማት ስራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ተጠየቀ