ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎችን ማሳካት ይጠበቅበታል

ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎችን ማሳካት ይጠበቅበታል

ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎች ላይ በትጋት በመረባረብ የዘመኑ አርበኛ መሆን እንደሚጠበቅበት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለፁ።

129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።

በዚሁ ጊዜ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እንደገለጹት፥ ጀግኖች አባቶችና እናቶች በወቅቱ የነበሩ የውስጥ ችግሮቻቸውን ወደ ጎን በመተው በአንድነት በመቆም የውጭ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ደማቅ ታሪክ ጽፈዋል።

የአሁኑ ትውልድ ከዓድዋ ድል ተባብሮ መስራትን በመማር በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ባሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች ላይ በንቃት በመረባረብና ከግብ በማድረስ የራሱን ድል ማስመዝገብ አለብት ሲሉም ገልጸዋል።

ትውልዱ እራሱን በትምህርትና በስነምግባር በማነጽ የሀገርን ኢኮኖሚ በመገንባት ተምሳሌት መሆን እንደሚጠበቅበትም እንዲሁ።

የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያውያን ባለፈ መላው የጥቁር ህዝቦች የሚኮሩበት ድል መሆኑንም አንስተዋል።(ኢዜአ)