ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎችን ማሳካት ይጠበቅበታል
ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎች ላይ በትጋት በመረባረብ የዘመኑ አርበኛ መሆን እንደሚጠበቅበት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለፁ።
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እንደገለጹት፥ ጀግኖች አባቶችና እናቶች በወቅቱ የነበሩ የውስጥ ችግሮቻቸውን ወደ ጎን በመተው በአንድነት በመቆም የውጭ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ደማቅ ታሪክ ጽፈዋል።
የአሁኑ ትውልድ ከዓድዋ ድል ተባብሮ መስራትን በመማር በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ባሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች ላይ በንቃት በመረባረብና ከግብ በማድረስ የራሱን ድል ማስመዝገብ አለብት ሲሉም ገልጸዋል።
ትውልዱ እራሱን በትምህርትና በስነምግባር በማነጽ የሀገርን ኢኮኖሚ በመገንባት ተምሳሌት መሆን እንደሚጠበቅበትም እንዲሁ።
የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያውያን ባለፈ መላው የጥቁር ህዝቦች የሚኮሩበት ድል መሆኑንም አንስተዋል።(ኢዜአ)

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል