ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎችን ማሳካት ይጠበቅበታል
ትውልዱ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የሰላምና ልማት ግንባታ ስራዎች ላይ በትጋት በመረባረብ የዘመኑ አርበኛ መሆን እንደሚጠበቅበት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለፁ።
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እንደገለጹት፥ ጀግኖች አባቶችና እናቶች በወቅቱ የነበሩ የውስጥ ችግሮቻቸውን ወደ ጎን በመተው በአንድነት በመቆም የውጭ ወራሪ ሃይልን በማሸነፍ ደማቅ ታሪክ ጽፈዋል።
የአሁኑ ትውልድ ከዓድዋ ድል ተባብሮ መስራትን በመማር በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ባሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች ላይ በንቃት በመረባረብና ከግብ በማድረስ የራሱን ድል ማስመዝገብ አለብት ሲሉም ገልጸዋል።
ትውልዱ እራሱን በትምህርትና በስነምግባር በማነጽ የሀገርን ኢኮኖሚ በመገንባት ተምሳሌት መሆን እንደሚጠበቅበትም እንዲሁ።
የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያውያን ባለፈ መላው የጥቁር ህዝቦች የሚኮሩበት ድል መሆኑንም አንስተዋል።(ኢዜአ)

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ