ምክር ቤቱ ታች ድረስ በመውረድ የክትትልና ቁጥጥር ስራ በመስራቱ የውሸት ሪፖርት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት ገለፀ
”አፊኒ” ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትን ከመደበኛ የፍትህ ተቋማት ጋር በቅንጅት የፍትህና እርቅ አገልግሎት እንዲሰጥ አዋጅ መዘጋጀቱም ተመልክቷል።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ በበጀት አመቱ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የዕቅድ ክንውን በጥብቅ እየተከታተለ ስለመሆኑ በማንሳት ግድፈቶች እንዲታረሙ እያደረገም ነው ብለዋል።
ከፅሁፍ ሪፖርቶች ይልቅ ተግባራትን ወረዳና ቀበሌ ድረስ በመውረድ እተመለከተ በመሆኑ የውሸት ሪፖርት መጠንን ዝቅ ማድረግ መቻሉን አረጋግጠዋል።
በአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች መካከል የስራ ፉክክር መንፈስ ለመፍጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መስሪያ ቤቶች ይሸለማሉ ብለዋል።
ህብረተሰቡን በሚገባው ልክ ተጠቃሚ ያላደረጉና ሀላፊነታቸውን ባልተገባ መልኩ የተጠቀሙ አመራሮች ላይ እርምጃ የክልሉ መንግሥት መውሰዱንም አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ