ምክር ቤቱ ታች ድረስ በመውረድ የክትትልና ቁጥጥር ስራ በመስራቱ የውሸት ሪፖርት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት ገለፀ
”አፊኒ” ባህላዊ የዳኝነት ስርዓትን ከመደበኛ የፍትህ ተቋማት ጋር በቅንጅት የፍትህና እርቅ አገልግሎት እንዲሰጥ አዋጅ መዘጋጀቱም ተመልክቷል።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ በበጀት አመቱ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የዕቅድ ክንውን በጥብቅ እየተከታተለ ስለመሆኑ በማንሳት ግድፈቶች እንዲታረሙ እያደረገም ነው ብለዋል።
ከፅሁፍ ሪፖርቶች ይልቅ ተግባራትን ወረዳና ቀበሌ ድረስ በመውረድ እተመለከተ በመሆኑ የውሸት ሪፖርት መጠንን ዝቅ ማድረግ መቻሉን አረጋግጠዋል።
በአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች መካከል የስራ ፉክክር መንፈስ ለመፍጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መስሪያ ቤቶች ይሸለማሉ ብለዋል።
ህብረተሰቡን በሚገባው ልክ ተጠቃሚ ያላደረጉና ሀላፊነታቸውን ባልተገባ መልኩ የተጠቀሙ አመራሮች ላይ እርምጃ የክልሉ መንግሥት መውሰዱንም አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል