በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት የተካነ እና ሥራ ፈጣሪ ዜጋን ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሣይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ክንውን አፈጻጸም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሔደ ነው።
የቢሮው ሀላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በሣይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎት የበቃ ህብረተሰብ ለመፈጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ቢሮው በክልሉ ያሉ ዞኖችና የክልል ማዕከላትን በቴክኖሎጂ ለማስተሣሰር እና የኮደርስ ስልጠናም በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑ አቶ ተካለኝ አስረድተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ምክር ቤት ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙ በበኩላቸው፤ ዓለም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ ለመቀላቀል በፈጠራ የተካነ ዜጋ በመፈጠር ድህነትንና ኋላ ቀርነትን ለመቅረፍ ሁሉም በትኩረት መሥራት እንዳለበት ተናግረዋል።
በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ተነሳሽነት የተጀመረውን የኮደርስ ስልጠና የክልሉ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ቢሮው የተጣለበትን ሀላፊነት በትኩረት እንዲወጣ ወ/ሮ እመቤት አስገንዝበዋል።
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በኮንሶ ዞን በመገምገም ላይ ነው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ከክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር ከክልሉ ሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ ሴቶች ስልጠና መስጠት ጀመረ
ምክር ቤቱ ታች ድረስ በመውረድ የክትትልና ቁጥጥር ስራ በመስራቱ የውሸት ሪፖርት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት ገለፀ
በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የህዝቡን የልማት ፍላጎት በሚመጥን መልኩ ምላሽ ለመስጠት አመራሩ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት የደቡብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት አሳሰበ