በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት የተካነ እና ሥራ ፈጣሪ ዜጋን ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሣይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ክንውን አፈጻጸም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሔደ ነው።
የቢሮው ሀላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በሣይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎት የበቃ ህብረተሰብ ለመፈጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ቢሮው በክልሉ ያሉ ዞኖችና የክልል ማዕከላትን በቴክኖሎጂ ለማስተሣሰር እና የኮደርስ ስልጠናም በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑ አቶ ተካለኝ አስረድተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ምክር ቤት ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙ በበኩላቸው፤ ዓለም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ ለመቀላቀል በፈጠራ የተካነ ዜጋ በመፈጠር ድህነትንና ኋላ ቀርነትን ለመቅረፍ ሁሉም በትኩረት መሥራት እንዳለበት ተናግረዋል።
በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ተነሳሽነት የተጀመረውን የኮደርስ ስልጠና የክልሉ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ቢሮው የተጣለበትን ሀላፊነት በትኩረት እንዲወጣ ወ/ሮ እመቤት አስገንዝበዋል።
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በኮንሶ ዞን በመገምገም ላይ ነው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ