በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት የተካነ እና ሥራ ፈጣሪ ዜጋን ለመፍጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሣይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ክንውን አፈጻጸም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሔደ ነው።
የቢሮው ሀላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በሣይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎት የበቃ ህብረተሰብ ለመፈጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ቢሮው በክልሉ ያሉ ዞኖችና የክልል ማዕከላትን በቴክኖሎጂ ለማስተሣሰር እና የኮደርስ ስልጠናም በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑ አቶ ተካለኝ አስረድተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ምክር ቤት ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙ በበኩላቸው፤ ዓለም በዲጂታል ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ ለመቀላቀል በፈጠራ የተካነ ዜጋ በመፈጠር ድህነትንና ኋላ ቀርነትን ለመቅረፍ ሁሉም በትኩረት መሥራት እንዳለበት ተናግረዋል።
በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ተነሳሽነት የተጀመረውን የኮደርስ ስልጠና የክልሉ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ቢሮው የተጣለበትን ሀላፊነት በትኩረት እንዲወጣ ወ/ሮ እመቤት አስገንዝበዋል።
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በኮንሶ ዞን በመገምገም ላይ ነው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል