የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው – ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
ሀዋሳ፡ የካቲት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ፡፡
የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ አመት 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ነው።
በምክር ቤቱ ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው።
ምክር ቤት በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁለንተናዊ እንቅሰቃሴዎችን የቅርብ ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ግብረ መልስና አቅጣጫ እየሰጠ ስለመሆኑም አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።
ከዛሬ ጀምሮ በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤው የባላፈውን ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ማፅደቅ፣ የበጀት አመቱን የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የግማሽ አመት አፈፃፀም በዝርዝር መገምገም። የገቢ ዕቅድ መከለስ፣ የክልሉን ተጨማሪ በጀት ማፅደቅ፣ አዋጆችንና ሹመቶችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
የዲዚን ህዝብ ባህል ታሪክና ማንነትን በጥናትና ምርምር በማስደገፍ ለትውልድ ማሰተላለፍ እንደሚገባ የዲዚና አካባቢዋ ምሁራን ማህበሩ የበላይ ጠባቂ አቶ መቱ አኩ ገለፁ
የሃገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
አርሶ አደሩ በእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ የኢኮኖሚ አቅሙን እንድያሳድግ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ