የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው – ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
ሀዋሳ፡ የካቲት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ፡፡
የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ አመት 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ነው።
በምክር ቤቱ ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው።
ምክር ቤት በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁለንተናዊ እንቅሰቃሴዎችን የቅርብ ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ግብረ መልስና አቅጣጫ እየሰጠ ስለመሆኑም አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።
ከዛሬ ጀምሮ በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤው የባላፈውን ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ማፅደቅ፣ የበጀት አመቱን የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የግማሽ አመት አፈፃፀም በዝርዝር መገምገም። የገቢ ዕቅድ መከለስ፣ የክልሉን ተጨማሪ በጀት ማፅደቅ፣ አዋጆችንና ሹመቶችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ