የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው – ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
ሀዋሳ፡ የካቲት 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ምክር ቤት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ፡፡
የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ አመት 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ነው።
በምክር ቤቱ ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እየሰራ ነው።
ምክር ቤት በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁለንተናዊ እንቅሰቃሴዎችን የቅርብ ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ግብረ መልስና አቅጣጫ እየሰጠ ስለመሆኑም አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።
ከዛሬ ጀምሮ በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤው የባላፈውን ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ማፅደቅ፣ የበጀት አመቱን የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የግማሽ አመት አፈፃፀም በዝርዝር መገምገም። የገቢ ዕቅድ መከለስ፣ የክልሉን ተጨማሪ በጀት ማፅደቅ፣ አዋጆችንና ሹመቶችን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ