የደቡብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉበኤ በዲመካ ከተማ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ የካቲት 18/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኦሞ ዞን ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ፣ 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉበኤ በዲመካ ከተማ መካሄድ ጀመረ።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አፈጉባኤ አቶ ሎስንዴ ሎኛሱዋ እንደገለፁት፥ የዞኑ ህዝብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ተረጋግጦ ፖለቲካዊ መስተጋብራቸው ከፍ እንዲል የምክር ቤት ከባላት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በዚህም የአስፈፃሚ መሥሪያ ቤቶች የሥራ ሪፖርታቸውን በመከታተል፣ ቁጥጥር በማድረግና ድጋፍ በመስጠት የተጣለባቸውን የህዝብ አደራ መወጣት እንዳለባቸውም አቶ ሎስንዴ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ምክር ቤቱ የደቡብ ኦሞ ዞን ሽግግር ም/ቤት 4ኛ ዙር፣ 11ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለ ጉባኤ መምርምሮ ማጽደቅ፣ የዞኑ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መርምሮ ማጽደቅ እና ስንብትና ሹመት ላይ በዝርዝር ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጀንካ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/