በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሱማሞ አካባቢ የሚገነባውን አየር ማረፊያ ግንባታን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
ሀዋሳ፡ የካቲት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን አረካ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታውን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአኑዋር ሰይድ ጠቅላላ ተቋራጭ፣ ሲ አር ቲ አማካሪና ባለሙያዎች እንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአረካ ከተማ አቅራቢያ በሱማሞ ሜዳ ለሚገነባው የአየር ማረፊያ ግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ በህዳር ወር ማውጣት ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ድርሻዬ ጋሻው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ