በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሱማሞ አካባቢ የሚገነባውን አየር ማረፊያ ግንባታን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
ሀዋሳ፡ የካቲት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን አረካ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታውን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአኑዋር ሰይድ ጠቅላላ ተቋራጭ፣ ሲ አር ቲ አማካሪና ባለሙያዎች እንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአረካ ከተማ አቅራቢያ በሱማሞ ሜዳ ለሚገነባው የአየር ማረፊያ ግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ በህዳር ወር ማውጣት ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ድርሻዬ ጋሻው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ