በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሱማሞ አካባቢ የሚገነባውን አየር ማረፊያ ግንባታን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
ሀዋሳ፡ የካቲት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን አረካ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታውን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአኑዋር ሰይድ ጠቅላላ ተቋራጭ፣ ሲ አር ቲ አማካሪና ባለሙያዎች እንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአረካ ከተማ አቅራቢያ በሱማሞ ሜዳ ለሚገነባው የአየር ማረፊያ ግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ በህዳር ወር ማውጣት ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ድርሻዬ ጋሻው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ