በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሱማሞ አካባቢ የሚገነባውን አየር ማረፊያ ግንባታን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት
ሀዋሳ፡ የካቲት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን አረካ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታውን የሚያስጀምር ልዑክ አረካ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአኑዋር ሰይድ ጠቅላላ ተቋራጭ፣ ሲ አር ቲ አማካሪና ባለሙያዎች እንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአረካ ከተማ አቅራቢያ በሱማሞ ሜዳ ለሚገነባው የአየር ማረፊያ ግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ በህዳር ወር ማውጣት ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ድርሻዬ ጋሻው – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
የህዝቡን የልማት ተሳትፎ በማጠናከር የከተማውን ዕድገት ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቦኖሻ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ
”እንዳይረሳ ቅድሚያ ለደኅንነት” በሚል መሪ ቃል የትራንስፖርትና መንገድ ዘርፍ የሕዝብ ንቅናቄ መድረክ ተካሄደ
ሚዲያው ለህብረተሰቡ የመረጃ ምንጭ ከመሆን ባለፈ የሚታዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በትኩረት መስራት እንዳለበት ተጠቆመ