የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃው ስነ ስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኤልያስ ዓለሙ የዛሬ ተመራቂዎች በትምህርት ጊዜያቸው ያሳዩትን ትጋት በስራቸውም በመድገም ህብረተሰቡን በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች አንድነትን በማጠናከር ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት የበኩሉን እንዲወጣ በክብር እንግዲነት የተገኙት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልደ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት በትምህርት ቆይታቸውን በቀሰሙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በታማኝነት እንደሚያገለግሉ ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ፣ በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ዘጋቢ፦ ውብሸት ኃ/ማርያም ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል