የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃው ስነ ስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኤልያስ ዓለሙ የዛሬ ተመራቂዎች በትምህርት ጊዜያቸው ያሳዩትን ትጋት በስራቸውም በመድገም ህብረተሰቡን በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች አንድነትን በማጠናከር ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት የበኩሉን እንዲወጣ በክብር እንግዲነት የተገኙት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልደ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት በትምህርት ቆይታቸውን በቀሰሙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በታማኝነት እንደሚያገለግሉ ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ፣ በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ዘጋቢ፦ ውብሸት ኃ/ማርያም ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች