የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃው ስነ ስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኤልያስ ዓለሙ የዛሬ ተመራቂዎች በትምህርት ጊዜያቸው ያሳዩትን ትጋት በስራቸውም በመድገም ህብረተሰቡን በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች አንድነትን በማጠናከር ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት የበኩሉን እንዲወጣ በክብር እንግዲነት የተገኙት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልደ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት በትምህርት ቆይታቸውን በቀሰሙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በታማኝነት እንደሚያገለግሉ ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ፣ በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ዘጋቢ፦ ውብሸት ኃ/ማርያም ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ