የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃው ስነ ስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኤልያስ ዓለሙ የዛሬ ተመራቂዎች በትምህርት ጊዜያቸው ያሳዩትን ትጋት በስራቸውም በመድገም ህብረተሰቡን በቅንነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች አንድነትን በማጠናከር ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት የበኩሉን እንዲወጣ በክብር እንግዲነት የተገኙት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልደ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት በትምህርት ቆይታቸውን በቀሰሙት ዕውቀት ህብረተሰቡን በታማኝነት እንደሚያገለግሉ ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ፣ በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ዘጋቢ፦ ውብሸት ኃ/ማርያም ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ