በሐዋሳ ከተማ ህዝባዊ ኮንፍራንስ እየተካሄደ ነው።
ሀዋሳ፣ የካቲት 15/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የብልጽግና ፓርቲ ”ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ቃል በ 2ተኛ መደበኛ ጉባኤ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ላይ የሚመክር ከተማ አቀፍ ህዝባዊ ኮንፍራንስ በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ውይይቱን የሚመሩት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ እና የቱሪዝም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሰላማዊት ካሳ ናቸው።
የብልጽግና ፓርቲ በምስራቅ አፍሪካ በርካታ አባል ያለው ግዙፍ ፓርቲ ነው ያሉት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ ከ 15 ሚሊየን በላይ አባላት አለው ብለዋል።
ፓርቲው ከፋፋይ ትርክቶችን በመተው ህብረብሔራዊ አንድነት ላይ አተኩሮ እየሰራ ያለ እውነተኛ ፓርቲ ስለመሆኑ ጠቁመው በተለይ የትላንት ቁርሾዎችንና ዕዳዎችን በመተው ምንዳዎችን ይዞ የቀጠለ ፓርቲ ነው ብለዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ለህዝቡ ቃል በገባው መሠረት ለቃሉ የታመነ እውነተኛ የህዝብ ፓርቲ ነው ያሉት ዶክተር ካሳሁን ኢትዮጵያ ከስንዴ ተመጽዋችነት ወደ ስንዴ ላኪነት ያሻገረ ፣ የማይቻሉ የሚመስሉ ህልሞች እውን ያደረገ ቃልንም ባህል ያደረገ ፓርቲ ነው ብለዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ከተመሠረተ የ 5 ዓመታት አጭር ዕድሜ ያስቆጠረ ቢሆንም በነዚህ ጥቂት አመታት አማላይ ስኬቶችን እያስመዘገበ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በውይይቱ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ባለፉት 7 ወራት በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ሪፖርት አቅርበዋል።
በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ምዕራፍ የተከፋፈለ የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
2ተኛው ምዕራፍ ከ 4 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ተመድቦ ከተማዋን ለማስዋብ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ከተማ አስተዳደሩ የውስጥ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ እየሰራ ነው ያሉት ከንቲባ መኩሪያ መርሻዬ እስካሁን የተሰበሰበው ገቢ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 596 ሚሊዮን ብር ብልጫ አለው ብለዋል።
ዘጋቢ :- አብደላ በድሩ
More Stories
በኩታ ገጠም እየተከናወነ ባለው የቡና እና ሌሎች ፍራፍሬ ምርት ተከላ ኢኒሼቲቭ የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት በአጭር ጊዜ እያሳደገ መምጣቱን በሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ከደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች እስከአሁን ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን በካፋ ዞን የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ህብረት ስራ ማህበራት በተደራጁበት ዓላማ ለአባሎቻቸው የተሟላ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ በጠንካራ አደረጃጀትና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት ሊደገፉ እንደሚገባ ተመላከተ