ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ መካሄድ ጀመረ፡፡
ሀዋሳ፣ የካቲት 15/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ መካሄድ ጀመረ
በኮንፈረንሱን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ኦርዲን በድሪ ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳደርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል ዶ/ር አብዱ ሁሴን፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክርቤት አባልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላን ጨምሮ ሌሎች በየደረጃው የሚገኙ የክልልና የዞን የከተማው አመራሮች፣የአገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች፣ወጣቶች በተገኙበት ነው ህዝባዊ ውይይት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ።
በቀጣይ የውይይቱ መድረኩ ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚነሱ ጥያቄዎች የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚና የፓርቲው ምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፈረንስ ከዛሬ ጀምሮ በ25 የተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡
ዘጋቢ:- ፋሲል ሀይሉ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ