ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ መካሄድ ጀመረ፡፡
ሀዋሳ፣ የካቲት 15/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ከተማ መካሄድ ጀመረ
በኮንፈረንሱን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ኦርዲን በድሪ ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳደርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል ዶ/ር አብዱ ሁሴን፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክርቤት አባልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ገብረመስቀል ጫላን ጨምሮ ሌሎች በየደረጃው የሚገኙ የክልልና የዞን የከተማው አመራሮች፣የአገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች፣ወጣቶች በተገኙበት ነው ህዝባዊ ውይይት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ።
በቀጣይ የውይይቱ መድረኩ ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚነሱ ጥያቄዎች የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚና የፓርቲው ምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፈረንስ ከዛሬ ጀምሮ በ25 የተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡
ዘጋቢ:- ፋሲል ሀይሉ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ