የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ
“የአካል ጉዳተኞችን የመሪነት ሚና በማጉላት አካታችና ዘላቂ ልማትን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ.ም የአካል ጉዳተኞች ቀን በዓል በአርባምንጭ ከተማ ተከብሯል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙ፤ በሀገራችን አካል ጉዳተኞች የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ህብረተሰቡም ማግለልና መድሎ በማቆም፣ አካል ጉዳተኝነት አለመቻል እንዳልሆነ በመገንዘብ ከጎናቸው እንዲሆንና ሁሉም ተቋማት የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ የዕቅዳቸው አካል አድርገው እንዲሰሩ ጭምር አሳስበዋል፡፡
የክልሉ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ደነቀ ዳሾ፤ የበዓሉ ዓላማ የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ስለ አካል ጉዳተኞች እና አካል ጉዳተኝነት በማስገንዘብ ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዋኖ ዋሎሌ፤ በዓሉ ሲከበር ቀደም ሲል የተሰሩ ስኬቶችን በማንሳትና በቀጣዩ ደግሞ ውጤታማ ስራ በመስራት ነው ብለዋል፡፡
ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮም አካል ጉዳተኞችን በሁሉም ረገድ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ የ10 ዓመት ዕቅድ በማዘጋጀት ግብ ጥሎ እየሰራ እንደሆነም አመላክተዋል፡፡
በአካል ጉዳተኞች ላይ ያሉ የተሳሳቱ አስተሳሰቦችን በመቅረፍ እኩል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በቅንጅት ልንሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ተሳታፊዎችም እንዲህ አይነት መድረኮች ለአካል ጉዳተኞች ወሳኝና መስራት እንደሚችሉ የሚያሳይና ህብረተሰቡም ግንዛቤ የሚያገኝበት በመሆኑ ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ብርሃኑ ዳሾ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ

More Stories
የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ውጤታማ የሆነ ስራ የሰራ አካባቢ ተጨማሪ ፕሮጀክት የማግኘት ዕድል አለው – ሚ/ር ዴኤታ የትምጌታ አስራት
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ10ኛ ጊዜ ያስተማራቸውን የሕክምና ዶክተሮችን እና የጤና ሳይንስ ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።