ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ
መምሪያው ለሴክተሩ ሠራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ባለሙያው ተቋሙ የተቋቋመለትን ዓላማ አውቆ ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን የጌዴኦ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ያሬድ በማብራራት፤ ሠራተኛው የዓመቱን ዕቅድ በማዘጋጀት በወርና በቀናት በመሸንሸን ተግባሩን እንዲያከናውን ታስቦ የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አክለውም መምሪያው ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው የተገኙ የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት የተቋማት ግንባታና የሪፎርም ስራዎች ቡድን መሪ አቶ መኮንን ጪጩ፤ በዞን ደረጃ ያሉት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት የክህሎት ክፍተት የሚሞላ ስልጠና በዕቅድ በመስጠት ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ባለሙያው ተግባሩን በዕቅድ ዝግጅት ማከናውን ይችል ዘንድ ከክልልና ከዞን ፐብሊክ ሰርቪስ ባገኙት ስልጠና መሰረት ሰነድ በማዘጋጀት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መስጠታቸውን በመምሪያው የልማት ዕቅድ በጀት ክትትል ግምገማ ግብረመልስ ቡድን መሪ አቶ ክብሩይስፋ ወጋየሁ በመናገር ሠራተኛውም ባገኘው ግንዛቤ ለተገልጋዩ እርካታ መስራት አለበት ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል