የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ።
ሀዋሳ፣ የካቲት 14/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራው ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ።
ልኡካን ቡድኑ አርባምንጭ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ የጋሞ ዞንና የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንድሁም የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎችና የኪነት ቡድን አባላት ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ልዑኩ በዛሬው ዕለት በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ይጎበኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፤ ፀሐይ ጎበና ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/