የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ።
ሀዋሳ፣ የካቲት 14/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራው ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ።
ልኡካን ቡድኑ አርባምንጭ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ የጋሞ ዞንና የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንድሁም የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎችና የኪነት ቡድን አባላት ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ልዑኩ በዛሬው ዕለት በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ይጎበኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፤ ፀሐይ ጎበና ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ