የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የፖሊዮ (የልጅነት ልምሻ) በሽታ መከላከያ ክትባት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በቀቤና ልዩ ወረዳ ፍቃዶ ጤና ኬላ አስጀመረ
ለአራት ቀናት የሚቆየው የክትባት ዘመቻ በሁሉም የክልሉ ዞኖች ልዩ ወረዳዎች የከተማና የወረዳ አስተዳደሮች እድሚያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ከአንድ ሚሊየን 48 ሺህ በላይ ህጻናት እንደሚከተቡ ተመላክቷል።
የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) በቫይረስ አማካኝነት የሚመጣና በዋናነት የህፃናትን ጤና በመጉዳት እስከሞት የሚያደርስ ሲሆን ክትባቱን በተገቢው መንገድ በመውሰድ በሽታውን መከላከል ይቻላል ተብሏል።
ክትባቱ በዘመቻ መልክ ቤት ለቤት በሚደረግ ጉብኝት የሚከናወን ሲሆን ሕፃናቱ ከአሁን በፊት ክትባቱን ቢከተቡም ባይከተቡም አሁን የሚሰጠውን የፖሊዮ ክትባት መውሰድ እንደሚኖርባቸው ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል