የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የፖሊዮ (የልጅነት ልምሻ) በሽታ መከላከያ ክትባት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በቀቤና ልዩ ወረዳ ፍቃዶ ጤና ኬላ አስጀመረ
ለአራት ቀናት የሚቆየው የክትባት ዘመቻ በሁሉም የክልሉ ዞኖች ልዩ ወረዳዎች የከተማና የወረዳ አስተዳደሮች እድሚያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ከአንድ ሚሊየን 48 ሺህ በላይ ህጻናት እንደሚከተቡ ተመላክቷል።
የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) በቫይረስ አማካኝነት የሚመጣና በዋናነት የህፃናትን ጤና በመጉዳት እስከሞት የሚያደርስ ሲሆን ክትባቱን በተገቢው መንገድ በመውሰድ በሽታውን መከላከል ይቻላል ተብሏል።
ክትባቱ በዘመቻ መልክ ቤት ለቤት በሚደረግ ጉብኝት የሚከናወን ሲሆን ሕፃናቱ ከአሁን በፊት ክትባቱን ቢከተቡም ባይከተቡም አሁን የሚሰጠውን የፖሊዮ ክትባት መውሰድ እንደሚኖርባቸው ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ