በክትባት ዘመቻው ከ552 ሺህ በላይ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ተደራሽ እንደሚሆንም ተመላክቷል።
በዕለቱ በታርጫ ከተማ ኢንላይት ህፃናት ትምህርት ቤት የክትባት ዘመቻውን ያስጀመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለፁት፤ ማህበራዊ ብልፅግና ማረጋገጥ የሚቻለው የዜጎችን ጤና በመጠበቅ ሲሆን በሽታውን መከላከል የመጀመሪያ ተግባር እና አክሞ ማዳን ደግም ቀጥሎ የሚመጣ ተግባር ነው።
የክትባት ዘመቻ ደግሞ በሽታን ለመከላከል ወሳኝ ተግባር በመሆኑ በሚካሄደው የፖሊዮ ዘመቻ ወላጆች፣ የአካባቢ ነዋሪዎችና የሚመለከታቸው አካላት ህፃናቱ ክትባት እንዲያገኙ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በሽታው በአንድ ቤት ከተከሰት በአካባቢው ሁሉ ሊሰራጭ ስለሚችል በአካባቢው ያሉ ህፃናትን ሁሉ በማስከተብ ወላጆች ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
የፖሊዮ በሽታን ከሀገራችን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት የመከላከያ ክትባትን ማስከተብና የአካባቢ ፅዳትንም ማጠናከር አስፈላጊ እንደሆነም አቶ ኢብራሂም አመላክተዋል
በክልሉ ክትባት ዘመቻ 552 ሺህ በላይ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ተደራሽ እንደሚሆኑም አቶ ኢብራሂም አስታውቀዋል፡፡
የዳውሮ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አስራት ቸርነት መከላከልና አክሞ ማዳን ላይ ትኩረቱን ባደረገው የጤና ፖሊሲያችን የመከላከያ ክትባት ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ሁሉም የሚመለከተው አካል በጉዳዩ ርብርብ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
የአካባቢ ፅዳት ተግባራትን በማጠናከር በሽታውን ለማጥፋት ወሳኝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንደሚሻ በመግለፅ በክትባት ዘመቻው ሁሉም ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ተደራሽ እንዲሆኑ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል በማለት አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል