አርሶ አደሮቹ የተለያዩ የውሃ አማራጮችን በመጠቀምና በቴክኖሎጅ በመታገዝ የተሻለ ምርታማ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን የአመያ ዙሪያ ወረዳ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ገልጿል፡፡
አርሶ አደር ደዋና ደርጫና ብዙነሽ በየነ የበጋ ስንዴ በመስኖ በኩታ ገጠም ያመረቱ አርሶ አደሮች ሲሆኑ የግብርና ቴክኖሎጂን በባለሙያ ዕገዛ በመተግበር ማምረታቸውን ተናግረዋል።
ማሳቸውን በሚገባ በማዘጋጀትና የመስኖ ውሃን በአግባቡ በመጠቀም እንዲሁም የተለየ እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የዘንድሮ የአየር ፀባይ ለበጋ የስንዴ ማሳ ምቹ በመሆኑ ከሄክታር እስከ 35 ኩንታል ማግኘት እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት የበጋ ወቅት የእርሻ ጊዜያቸውን ባለመጠቀማቸው የሚቆጩት አምራቾቹ ዘንድሮ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ ወደ ማምረት በመግባታቸው በትንሽ መሬት የተሻለ ምርት በማምረት ከፍተኛ ገንዘብ እያገኙ መሆናቸውን አክለዋል።
የወረዳው ግብርና፣ አካባብ ጥበቃና ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን ዳዕሞ ባለፉት አመታት መደበኛና የበጋ መስኖ ያልተለመደና የማይታወቅ ቢሆንም በዚህ ጥቂት አመታት በስንዴ ልማት የተሻለ ምርት ከማግኘት ባለፈ ተግባሩም እየሰፋ መሆኑን ተናግረው በጓሮ አትክልት የመደበኛ መስኖ ሥራ ውጤት ከመመዝገቡ ያለፈ አርሶ አደሩ ሀብት እያፈራ መሆኑን አክለዋል።
አዘጋጅ አብዮት እሸቱ ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል