የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ጋርሾ እና የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ዘመቻውን በኬሌ ከተማ በይፋ አስጀምረዋል።
በዞኑ ከ36 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህጻናት የፖሊዮ ክትባት ለማድረስ ታቅዶ ለሁለት ተከታታይ ወራት ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት የኮሬ ዞን ጤና ዩኒት ኃላፊ አቶ ደመላሽ ሽፈራው፤ በቂ ዝግጅት በመደረጉ የተሸለ ውጤት እንጠብቃለን ብለዋል።
የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ በኩላቸው፤ ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ህጻናት እየተሰጠ ላለው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የዞኑ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለው ክትባቱ በትኩረት መሠጠት እንዳለበት አመላክተዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብር የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ጋርሾ በበኩላቸው፤ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ዓላማው ከሀገራችን ፖሊዮን ማጥፋት መሆኑን ተናግረው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች እየተሠጠ መሆኑን ገልጸዋል።
አንድም ህጻን ሳይከተብ መቅረት የለበትም ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው ለዚህም ነው ዘመቻው ቤት ለቤት እንየተደረገ ያለው ብለዋል።
ከፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ጎን ለጎን የህጻናት የምግብ እጥረት፣ የነፍሰ ጡር እናቶች፣ የቆልማማ እግር እና ፖሊዮ የተገኘባቸውም ካሉ የመለየት ስራ የሚሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ሌሎች የዞኑና የኬሌ ከተማ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ዘመቻው ከ14/06/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ
ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማሳደግና ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሀገሪቱ ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ተገለፀ