የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ጋርሾ እና የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ዘመቻውን በኬሌ ከተማ በይፋ አስጀምረዋል።
በዞኑ ከ36 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህጻናት የፖሊዮ ክትባት ለማድረስ ታቅዶ ለሁለት ተከታታይ ወራት ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት የኮሬ ዞን ጤና ዩኒት ኃላፊ አቶ ደመላሽ ሽፈራው፤ በቂ ዝግጅት በመደረጉ የተሸለ ውጤት እንጠብቃለን ብለዋል።
የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ በኩላቸው፤ ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ህጻናት እየተሰጠ ላለው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የዞኑ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለው ክትባቱ በትኩረት መሠጠት እንዳለበት አመላክተዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብር የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ጋርሾ በበኩላቸው፤ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ዓላማው ከሀገራችን ፖሊዮን ማጥፋት መሆኑን ተናግረው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች እየተሠጠ መሆኑን ገልጸዋል።
አንድም ህጻን ሳይከተብ መቅረት የለበትም ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው ለዚህም ነው ዘመቻው ቤት ለቤት እንየተደረገ ያለው ብለዋል።
ከፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ጎን ለጎን የህጻናት የምግብ እጥረት፣ የነፍሰ ጡር እናቶች፣ የቆልማማ እግር እና ፖሊዮ የተገኘባቸውም ካሉ የመለየት ስራ የሚሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ሌሎች የዞኑና የኬሌ ከተማ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ዘመቻው ከ14/06/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

 
                 
                                         
                                         
                                         
                                        
More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ