የተለያዩ የልማት ፍላጎቶችንና ጥያቄዎችን ለመመለስ እንዲያስችል የገቢ አፈጻጸሙን በይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
መምሪያው በ2017 በጀት አመት ሰባት ወራት ከ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሠብሰብ መቻሉም ተመልክቷል።
”ቃልን ወደ ባህል፤ ጸጋን ወደ ገቢ” በሚል መሪ ቃል የታክስ ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ልሳነ ወርቅ ካሳዬ የንቅናቄ መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት፤ የተለያዩ የልማት ፍላጎቶችንና ጥያቄዎችን ለመመለስ እንዲያስችል ያሉንን ጸጋዎች በመለየት የገቢ አቅማችንን በይበልጥ ማሳደግ ይገባናል።
መምሪያው በበጀት አመቱ 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ለመሠብሰብ አቅዶ እየሰራ መሆኑንና በሰባት ወራት 2 ቢሊዮን 652 ሚሊዮን 898 ሺህ 916 ብር ገቢ መሠብሰቡን ተናግረዋል።
የዕቅዱ አፈጻጸም ካለን አቅም አንጻር ሲታይ ዝቅተኛ በመሆኑ በቀጣይ ቀሪ ወራት ያለንን አቅም አሟጠን በመጠቀምና ሁሉንም የገቢ አማራጮች በይበልጥ በመለየት መሰብሰብ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ዞኑ ሰላማዊ አካባቢ ከመሆኑ ባሻገር የማዕድናት ክምችት ባለቤት፣ ለኢንዱስትሪና ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለንግድ እንቅስቃሴና ለግብይት ምቹ በመሆኑ የገቢ እቅዱን የተሳካ ለማድረግ በሁሉም መዋቅር በይበልጥ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ወ/ሮ ልሳነ ወርቅ።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የተለያዩ የልማት ፍላጎቶችንና ጥያቄዎችን ለመመለስ እንዲያስችል የገቢ አፈጻጸሙን በይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
 
                
 
                                         
                                         
                                         
                                        
More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ