የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: የካቲት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከየካቲት 12 -13/2017 ዓ.ም ድረስ በወልቂጤ ከተማ ያካሒዳል።
ምክር ቤቱ የባለፈውን 6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ የሚጀምር ሲሆን፥ የክልሉን መስተዳድር ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ምክር ቤቱ በሚኖረው ቆይታ በሌሎች ተጨማሪ አጀንዳዎች ዙሪያ መክሮ ውሳኔዎችን ያሳልፋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ