የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: የካቲት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከየካቲት 12 -13/2017 ዓ.ም ድረስ በወልቂጤ ከተማ ያካሒዳል።
ምክር ቤቱ የባለፈውን 6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ የሚጀምር ሲሆን፥ የክልሉን መስተዳድር ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ምክር ቤቱ በሚኖረው ቆይታ በሌሎች ተጨማሪ አጀንዳዎች ዙሪያ መክሮ ውሳኔዎችን ያሳልፋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ