የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: የካቲት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከየካቲት 12 -13/2017 ዓ.ም ድረስ በወልቂጤ ከተማ ያካሒዳል።
ምክር ቤቱ የባለፈውን 6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ የሚጀምር ሲሆን፥ የክልሉን መስተዳድር ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ምክር ቤቱ በሚኖረው ቆይታ በሌሎች ተጨማሪ አጀንዳዎች ዙሪያ መክሮ ውሳኔዎችን ያሳልፋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ