የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: የካቲት 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከየካቲት 12 -13/2017 ዓ.ም ድረስ በወልቂጤ ከተማ ያካሒዳል።
ምክር ቤቱ የባለፈውን 6ኛ ዙር 4ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ የሚጀምር ሲሆን፥ የክልሉን መስተዳድር ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ምክር ቤቱ በሚኖረው ቆይታ በሌሎች ተጨማሪ አጀንዳዎች ዙሪያ መክሮ ውሳኔዎችን ያሳልፋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ