የኮሬ ዞን በደን የተሸፈኑ ሰንሰለታማ ተራሮች ያሉት ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግሮች እየወደመ ይገኛል።
አቶ ዘብዴዎስ ሽብሩ በኮሬ ዞን የደን እና አካባቢ ጥበቃ ዩኒት የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቡድን መሪ እና የጽ/ቤቱ ተወካይ እንደተናገሩት፣ ጽ/ቤቱ በደን ልማት፣ በብዝሃ ሕይወት እና አካባቢ ጥበቃ ላይ በትኩረት ይሠራል።
በዞኑ በተፈጥሮ ያሉ ደኖች ተከልለው እንዲጠበቁ በተሠራው ሥራ ዘንድሮ አምስት የሚሆኑ የደን ሥፍራዎችን ማካለል መቻሉንና ይህም በህገ-ወጥ መንገድ ደንን በሚወሩ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ አጋዥ መሆኑን አመላክተዋል።
ሌሎች የደን ሥፍራዎችን ለማካለል እየተሠራ ነው የሚሉት አቶ ዘብዴዎስ፣ ህግን ለማሥከበር እየተሠራ ባለው ሥራ ከ3 መቶ 50 በላይ ህገ-ወጦችን እርምጃ ለማስወሰድ በሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ያለ ደን የሰው ልጆችን ጨምሮ ብዝሃ ሕይወት የማይታሰብ በመሆኑ ደንን በመጠበቅ ሕይወትን ለማስቀጠል ከዞን አስተዳደር ጋር በመተባበር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ስለመሠራታቸው አመላክተዋል።
አሁን ላይ ወቅቱ በጋ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሰደድ እሳት ስጋት በመኖሩ ሕብረተሰቡ ለደኖች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ያሉት የቡድን መሪው፣ ቀደም ተብሎ ግንዛቤ የተፈጠረ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ለዚህ የተቋቋሙ 12 ግብረ ኃይሎች በሥራ ላይ መሆናቸውን ያመላከቱ ሲሆን የሰደድ እሳቱ ድንገት ቢከሰት ሳይዛመት ተረባርቦ መቆጣጠር ላይ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ለስጋቱ ሰሞኑን በዞኑ ዞቄሳ ቀበሌ ተከስቶ የነበረውን ሕብረተሰቡ ተረባርቦ ተጨማሪ ውድመት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን እንደማሣያ ጠቁመዋል።
ነዋሪዎች ማንኛውንም እሳት ሲያቀጣጥሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውና ደንን እንዲጠብቁ አሳስበዋል።
ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ